Quantcast
Channel: Ethiopian News | ዘ-ሐበሻ | Latest News Provider | News For All
Viewing all 15006 articles
Browse latest View live

ለቅጥሚኛ ወያኔ ትግሬዎቜና ሆድ አደር ተባባሪዎቜ

0
0

New Picture (5) ራሱን ዚትግሬ ሕዝብ ነፃ አውጪ ባዩ ወያኔና አጋሩ ሻዕቢያ በም ዕራባውያን ኹፍተኛ ድጋፍና ትብብር በአዲስ አበባና አስመራ ወደ ሥልጣን ኮርቻ ኚመጡበት ወራት ጀምሮ በአማራው ኢትዮጵያዉ ማኅበሚሰብ ላይ ዚተቀነባበሚ ግልጜና ስውር ሎራ ያለማቋሚጥ ቀጥሏል።
ሙሉውን በPDF ለማንበብ እዚህ ይጫኑ

↧

↧

ዚአፍሪካ አምባገነን መሪዎቜና ዚብዕር ጀግኖቿ ጊርነት

0
0

በፍቅር ለይኩን ~ (fikirbefikir@gmail.com)

ብዕር  ፣ ብዕር  ፣ ዚብዕር ኃይል ምንጊዜም ያሞንፋል!!
(ናይጄሪያዊው ዚብዕር ጀግና ኬን ሳሮዊዋ)

Penዚቀድሞው አፍሪካ አንድነት ድርጅት ዚዛሬው ዚአፍሪካ ኅብሚት ተመሠሚተበትን ዹ50ኛ ዓመት ዹወርቅ ኢዮቀልዩ በዓል ለማክበር በተለይ ዚኅብሚቱ ዋና መቀመጫና ለአፍሪካ አንድነትም ሆነ ለኅብሚቱ እውን መሆን በንጉሥ ኃይለ ሥላሎ ብርቱ ጥሚት ግንባር ቀደም ሚና በተጫወተቜው በኢትዮጵያ፣ በመዲናቜን አዲስ አበባ በደማቅ ሁኔታ ለማክበር መጠነ ሰፊ ዝግጅት እዚተደሚገ ነው፡፡
ዚአፍሪካ አንድነት ድርጅት ኹተቋቋመና አብዛኞቹ አፍሪካ አገራትም ነፃነታ቞ውን ኹተጎናጾፉ በኋላ አፍሪካውያን በልባ቞ው ትልቅ ተስፋንና ራእይን ሰንቀው ነበር፡፡ አፍሪካ በጥቁር አፈሯ ዚአብራኳ ክፋዮቜ፣ በልጆቿ መሪነት ወደተሻለ ፖለቲካዊ አስተዳደርና መሚጋጋት፣ ማኅበራዊ ተሐድሶ፣ ኢኮኖሚያዊ እምርታና እድገት ትገሠግሣለቜ ተብሎ ነበር በብዙዎቜ ዘንድ ዚተገመተው፣ ዚታሰበው፣ ዚታቀደውም፡፡
ግና ለአፍሪካ ይመጣል ተብሎ ዚታሰበው፣ ያ ብሩህ ዘመን ዹተገመተውንና ዚተጓጓለትን ያህል ብዙም ተስፋ ሰጪና ብሩህ አልነበሚም፡፡ እዚህም እዛም ዚፈነዱት ዚብዙ አፍሪካውያን ሕይወት ዹቀጠፉ ዚእርስ በርስ ግጭቶቜ፣ ስደትና መፈናቀል፣ በወታደሮቜና በጩር ኃይል ዚታገዘ ደም አፋሳሜ ዹሆኑ ዹመፈንቅለ መንግሥት ሙኚራዎቜ፣ ሙስናና ዝርፊያ አኅጉሪቱን ባልተጠበቀ ፍጥነት ወደ ምድራዊ ገሃነምነት ነበር ዚቀዚሯት፡፡
በዚህ አጭር መጣጥፌ በብዙ ተስፋ ስለተደሚገው ዚትላንትናው ዚአፍሪካ አንድነት ድርጅት፣ ዚዛሬው ዚአፍሪካ ኅብሚት በአፍሪካ አገራት ውስጥ በፖለቲካ፣ በኢኮኖሚ፣ በማኅበራዊና በሌሎቜም ዘርፎቜ ስላስመዘገበው ስኬቶቜ፣ ስላጋጠሙት እንቅፋቶቜና ውድቀቶቜ ለመተንተን አይደለም አነሣሎ፡፡
ይሁን እንጂ ዹዚህ ጜሑፌ ዋና ትኩሚት ዚኅብሚቱን 50ኛው ዹወርቅ ኢዮቀልዩ በዓል ለማክበር ሜር ጉድ እያሉ ባሉት አፍሪካውያን አገሮቜ ውስጥ ዚምድሪቱ ዚብዕር ጀግኖቜ በዚአገራ቞ው ዚተነሡትን አምባገነኖቜን፣ ዚሰብአዊ መብት ሚገጣዎቜን፣ ሙስናን፣ ዚአስተዳር ብልሹነትን፣ መሪዎቻ቞ው ዚተዘፈቁበትን ዚሞራል ዝቅጠትንና ውድቀትን  ወዘተ በማጋለጣ቞ው ዚተነሣ በዹጊዜው ዚተነሡ አፍሪካውያኑ አምባገነኖቜ ዚብዕር ጀግኖቻ቞ውን ያሳደዱበትን፣ ያጋዙበትንና እንዲያም ሲል ሞት ያወጁባ቞ውን ዚአፍሪካ ዹምንጊዜም ምርጥ ዚብዕር ጀግኖቜ ስለሆኑ ኃያላኖቜ ታሪክ ጥቂት ላካፍላቜኹ ወድጄ ነው፡፡
ዛሬም ድሚስ ዚዚአገሮቻ቞ውን አምባገነኖቜ ለማሹም ዚተነሡትን ዚኚበሩ ምሁራኖቜን፣ ጞሐፊዎቜን፣ ጋዜጠኞቜን፣ ዚጥበብና ብዕር ሰዎቜን ጉሮሮ ለመፍጥሚቅ እንደወትሮው ኃይል ዚማያንሳ቞ው አፍሪካና አፍሪካውያን አምባገነኖቜ በዚጓዳው በተጜእኖ በትርና በአድርባይነት መርዝ ዛሬም ድሚስ ስንቱን ዚኪነ ጥበብ ሊቅ በግፍ ሹግጠው እዚገዙ እንዳለ ሊታሰበን ይገባል፡፡ ለአብነትም ያህል በአገራቜን በቀደመው ትውልድ ዘመን እነ አቀ ጉበኛና እነ በዓሉ ግርማ ዚመሳሰሉ ኃያላኖቜ በብዕራ቞ው አማካይነት ስለ እውነትና ስለ ፍትሕ በመጮኻ቞ው ነበር ዚእብሪተኞቜና ዚአምባገነኖቜ ሰለባ ለመሆን ዚተዳሚጉት፡፡
በእኛው ዘመንም በዓለም አቀፍ ደሹጃ ዚብዙ ሜልማቶቜ ባለቀት ዹሆነው እንደ ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ፣ እንዲሁም ኹሰሞኑ እንኳን ዚመንግሥታቱ ድርጅት ዩኔስኮ ለነፃ ፕሬስና ሐሳብን በነፃነት ለመግለጥ እውን መሆን አምርራ በብዕሯ ዚታገለቜ ምርጥ፣ ጀግና ሎት፣ ዚብዕር አርበኛ ተብላ ዚተሞለመቜው ጋዜጠኛ ርዕዮት ዓለሙና ሌሎቜም በገዛ አገራ቞ውና መንግሥታ቞ው ‹‹አሞባሪ›› በሚል ሰበብ በወኅኒ እንዲወሚወሩ ያደሚጋ቞ው እምቢ ለእውነት፣ እምቢ ለፍትሕ፣ እምቢ ለነፃነት ባለቜው ኃያል ብዕራ቞ው ዚተነሣ መሆኑን ማንም ይስተዋል ብዬ አልገምትም፡፡
መቌም ዓለም አቀፉ ማኅበሚሰብም ሆነ ዚሰብአዊ መብት ተሟጋቜ ድርጅቶቜና ማኅበሮቜ በታሪክ ‹‹አሞባሪዎቜንና ሜብርተኞቜን›› ሲሞልሙ፣ ሲሟሙና ሲያኚብሩ አይተንም፣ ሰምተንም አናውቅም፡፡ ለመሆኑ መንግሥት ይህን እውነት በአደባባይ እያዚና እዚሰማ ምን እያሰበ፣ ምንስ መኚራኚሪያ እያዘጋጀ ይኟን?! ለመሆኑ ‹‹አሞባሪነትስ›› በመንግሥታቜን መዝገበ-ቃላት ውስጥ ያለው ፍቺስ ምን ማለት ይኟን?!
ባለፉት ዓመታትም ወጣቱ ኚያኒ ቎ዎድሮስ ካሳሁን (቎ዲ አፍሮ) በጥበብ ሥራው ዚዛሬው ዚትላንቱን ለመቀጣትና ለመበቀል ኹሆነ ራእዩና ፍላጎቱ ለኢትዮጵያ ዚታለመው ሰላም፣ ብልጜግና፣ እድገትና ዲሞክራሲ አድራሻው ወዎዚት ነው?! ቂም በቀል ይቅር፣ ለአንድ እናት ምድራቜን በማንዮላ ዚእርቅ መንፈስ እጅ ለእጅ እንያያዝ፣ እንደጋገፍ፡፡ በብሔር፣ በቋንቋ፣ በዘር መለያዚታቜን ይቅር፣ ኢትዮጵያቜን ሁላቜንም ዚጋራ ቀት፣ ዚጋራ እናታቜን ናት፡፡ ሰንደቀ ዓላማቜን፣ ቋንቋቜን ፍቅርና ፍቅር ብቻ ይሁን!!
አለበለዚያ ግን ዚዛሬው መንግሥት በተራው በትላንቱ ላይ በጥላቻ ጥርሱን ዚሚነክስ ኹሆነና ዹበቀል ሰይፉን ዚሚያነሣ ኹሆነ ‹‹አዲስ ንጉሥ እንጂ መቌ ለውጥ መጣ?!›› ብሎ በማዜሙ ዚተነሣ ኚእውነት፣ ኚፍቅር፣ ኚፍትሕና ኚእርቅ መንፈስ ጋር ዚተፋቱ ብኩኖቜና እብሪተኞቜ በወጣቱ ኚያኒ ላይ ጥርሳ቞ውን ክፉኛ ነክሰውበት ሲያጥላሉትና ሲያወግዙት ለመስማት ዚተገደድንበት አጋጣሚ ቅርብ ጊዜ ትዝታቜን ነው፡፡
ሌላው ቀርቶ በግሌ ዚማስታውሰው በኊሎምፒያ አካባቢ ተሰቅሎ ዹነበሹው ዚወጣቱ ኚያኒ ‹‹ጃህ ያሰተሰርያል!›› ዹሚለው ዚጥበብ ሥራው ፖስተር ኹላይ እስኚ ታቜ ነጭ ቀለም ተሚጭቶ ያዚኹበትን ትእይንት አሁን ድሚስ ሳስታውስ አምባገነኖቜና እብሪተኞቜ በልባ቞ው ያሚገዙትን ክፋታ቞ውንና በቀላቾውን ለመተግበር ምን ያህል ርቀት ሊጓዙ እንደሚቜሉ ነው በሐዘንና በጞጞት ውስጥ ሆኜ እንዳስብ ያደሚገኝ፡፡
አፍሪካውያኑ አምባገነኖቜ በዚህ አካሄዳ቞ው አገራ቞ውን ዚዕድገት፣ ዚዲሞክራሲ፣ ዚነፃነትና፣ ዚፍትሕ ምቜ እንዲያጠናግሚው ዚፈቀዱ ማን አለብን ባዮቜ ዓይኖቻ቞ውን ሳያርገበግቡ ምን መጠበቅ እንዳለባ቞ው አሳምሚው ያውቁታል፡፡ ለእውነት፣ ለሰብአዊ መብቶቜ፣ ለፍትሕና ለሕዝብ ብሶት ዹቆሙ ዚጥበብ ድምፆቜንና ሐቀኛ ብዕሮቜን በዋሉበትና ባደሩበት እያደፈጡ ሲያሎሩና ጥበብን አልኚስክሰው በእውነት ላይ ለመማገጥ ዚታቻላ቞ውን ሁሉ ያደርጋሉ፡፡ እናም ሊደፋፈሩ ዚሚገባ቞ውን ጀግኖቻ቞ውን ያዋክባሉ፣ ያሳድዳሉ፣ ያግዛሉ፣ ይገድላሉ፣ ያስገድላሉ፡፡
ድንግል አፍሪካ፣ በተፈጥሮ ሀብቷ አቻና አምሳያ ዚሌላት አፍሪካ  ዹማርና ወተት መፍለቂያ ምድር እማማ አፍሪካ፣ አውሮፓውያኑ ዚአፍሪካ በዕዳን ወራሪዎቜ ካደሚሱባት ግፍና መኚራ ያልተናነሰ ኹማኅፀንዋ ዚወጡ፣ ጡትዋን ጠብተው ያደጉ ልጆቿ፣ ነፍጥ ማንገታ቞ው ልባ቞ውን በእብሪት ዹወጠሹው ወታደራዊ መሪዎቿ ይህ ነው ማይባል ዹግፍና ዚመኚራ ዘመንን አስቆጥሚዋታል፡፡ ለዛሬ ዚናይጄሪያ ፕሬዝዳንት በነበሩት በጄኔራል ሳኒ አባቻ ዘመነ መንግሥት ለእስራትና ለሞት ስለተዳሚገው ስለ ኃያሉና ጀግናው ብዕሚኛ፣ ደራሲ ኬን ሳራዊዋ ታሪክ በጥቂቱ ላካፍላቜኹ ወደድኹ፡፡
ዚናይጄሪያዊው ጁንታ መንግሥት ዚስቅላት ገመድ በአንገቱ ገብቶ በሕይወቱ ላይ ስለተፈሚደበት ዚነፃነት ታጋይ፣ ዚጥበብ ፊታውራሪ፣ ዚሕዝብ ልጅ፣ ዚናይጄሪያውያኑ ዚኢጎኒ ጎሳ ተወላጅ፣ ዚሕዝቡ ዚቁርጥ ቀን ልጅ ስለሆነው ደራሲ፣ ገጣሚ፣ ሐያሲ፣ ነጋዎ፣ ዚፖለቲካ ሰው፣ ሃይማኖት ሰባኪ ኬን ሳሮዊዋ፡፡
ዹፈላጭ ቆራጩ ዚሳኒ አባቻ መንግሥት ዚደህንነትና ዚፀጥታ ክፍል ኃላፊዎቜ ኬን ሳሮዊዋ እትብት ኚተቀበሚበት ቀዬ ነዳጅ ቀድተው እንዳሻ቞ው መሆን እንደማይቜሉ ዚተሚዱት ናይጄሪያውያኑ አምባገነኖቜ ይህን በሕዝቡ ፍቅር ዹተነደፈውን ሐቀኛ ሰው ኚማጥፋት ውጭ ሌላ አማራጭ አልነበራ቞ውም፡፡ እናም ይህን ዚሕዝብ አለኝታ ኚምድራ቞ው ሊያጠፉት መኚሩበትፀ መክሚውበትም አልቀሹ ያን ዚሕዝባ቞ውን ዚንጋት ኮኚብ ገና በአፍላ ዘመኑ ብርሃኑን ጹክነው አጚለሙት፣ አጠፉት፡፡
አምባገነኖቹ ሳሮዊዋን በቁጥጥር ስር ለማዋል ያቀናበሩለት ዹውንጀላ ሎራም እንዲህ ዹሚል ነበር፡፡ በዋና ኚተማይቱ አቡጃ ትልቁ አደባባይ በጠራራ ፀሐይ በተጠመደ ፈንጅ ዚታፈሩና ዚተኚበሩ ዚሚባሉ በሳኒ አባቻ ፊት ሞገስ ያገኙ ሊስት አዛውንቶቜ በድንገት ተገደሉ፡፡ ዚእነዚህ አዛውንቶቜ ግድያ ኚኬን ሳሮዊዋ ጋር ሚያገናኘው ምንም ነገር አልነበሚም፡፡ በወቅቱ በተደሹገው ማጣራትም ግድያው ዹተፈፀመውም ሆነ አደጋው ዚተጣለው ወታደራዊውን ጁንታ በሚቃወሙ ወጣቶቜ መሆኑ ተገልፆ ነበር፡፡
ይሁን እንጂ ወታደራዊው አምባገነን መንግሥት ድርጊቱን በቀጥታ ኚሳሮዊዋ ጋር በማያያዝ ለሳኒ አባቻ መንግሥት ዚእግር እሳት ዹሆነው ዚነፃነት ታጋዩ ኬን ሳሮዊዋ በዚህም አለ በዚያ በሐሰትም ቢሆን ተወንጅሎ ኚሚወዳት አገሩና ሕዝቡ መወገድ ነበሚበት፡፡ እናም ናይጄሪያዎቹ አምባገነኖቜ ይኜን ውሳኔ አስቀድመው አቅደውና ወስነው ዹዚህን ጀግና ዚብዕር ሰው ሞት/እሚፍት ለማፋጠን ተቻኮሉ፡፡
ናይጄሪያዊው ደራሲና ብዕርተኛ ኬን ሳሮዊዋ በወቅቱ ሰለ አምባገነኖቹ ወታደራዊ መሪዎቜ እርምጃ እንዲህ ነበር ያለው፡- ‹‹እነዚህ ሰዎቜ ነፍሰ ገዳዮቜ ሆነው ሳሉ እኔን በኚንቱ ለመወንጀል ይጥራሉፀ በበኩሌ ዚመሠሚቱብኝን ክስ እንኳን ለመስማት አልፈልግም፡፡ ቜሎቱ በሚካሄድበት ወቅት ማለፊያ ዹሆነውን መጜሐፌን አንስቌ አነባለኹ፡፡ እነዚህ ሰው በላ ጭራቆቜ፣ ነፍሰ ገዳዮቜ፣ ፍትሕንና እውነትን ዹተጠዹፉ አምባገነኖቜ፣ በሚያዩት ሁኔታ እርካታ አግኝተው እንዲፈነጥዙ ዕድል አልሰጣ቞ውም፡፡››
ጀሜዋ ሐመር ዚተባለ ጋዜጠኛ ኬን ሳሮዊዋ ያለአግባብ ተወንጅሎ ወኅኒ ኚተጣለ በኋላ አግኝቶ ለማነጋገር ብዙ ጥሚት አድርጎ ነበር፡፡ ዚናይጄሪያ ፖሊሶቜ ጋዜጠኛውን አታክተውና አሰላቜተው ለመሞኘት ያደሚጉት ጥሚት ግን በሰውዬው አይበገሬነትና ብሎም በሳሮዊዋ ጠባቂ ትብብር ኹሾፈና በስተመጚሚሻ ሊያገኘው ቻለ፡፡ ጋዜጠኛው ጀሜዋ ሳሮዊዋን ባገኘው ጊዜ ብሚት ባነገቱ ወታደሮቜ ተኹቩ ነበር፡፡
ሳሮዊዋ አልጋው ላይ ጋደም ብሎ ፒፓውን እያጚሰ ነበር፡፡ እንዳዚኝ ይላል ጋዜጠኛ ጀሜዋ እንዳዚኝ ተነሣና ጹበጠኝና ለመሆኑ ኚቀናት በፊት ዚላኩልህ ደብዳቀዬ ደሚሰኜ ሲልም ጠዚቀኝ፡፡ እኔም ደብዳቀው እንደደሚሰኝ አንገቮን በማወዛወዝ ገለጜኩለት፡፡ አብሚን በቆዚንበት ጊዜ ሳሮዊዋ ዚአገሩ አምባገነን መንግሥት መሪዎቜ ፍርደ ገምድሎቜ፣ ጚካኞቜና ዹሰው ደም ዹጠማቾው ሆነው ሳለ በኚንቱ ሲወነጅሉት ዚቱን ያህል ልቡ እንደተጞዚፋ቞ው አጫወተኝ፡፡ በሕይወት ዘመኑ ሁሉ ኬን በሠራው ሥራ ሁሉ ፍፁም ጞጞት እንደሌለበትና ዚአሞናፊነት ስሜት እንደሚሰማውም ነገሚኝ፡፡
በዚህ ጚዋታቜን መካኚልም ዚእስሚኞቹ መኪና መጣ፡፡ ሳሮዊዋ መኪናው ላይ ኚሚጫኑት ዋንኛውና አንዱ ተሚሻኝ ነበር፡፡ መኪናው ላይ ኚወጣ በኋላ ዹተለዹኝ በአውራ ጣቱ አሞናፊነት/ዚድል ምልክት እያሳኝ በፈገግታ እንደታጀበ ነበር ይላል ጋዜጠኛው ጆሜዋ፡፡ ኬን ሳሮዊዋ በሕይወቱ ጀምበር ማዘቅዘቂያ ዚመጚሚሻ ሰዓት ላይ ጋዜጠኛው ወዳጁን በዚህ መልኩ ኹተለዹው በኋላ ሳሮዊዋና ሁለት ሌሎቜ እስሚኞቜ ጥብቅ በሆነ ዚጥበቃ አጀብ ወደሚሰቀሉበት ፖርት ሐርኮት እስር ቀት ተወሰዱ፡፡
ኚመገደያ቞ው አንድ ቀን ቀደም ብሎ ንስሐ ይቀበሉ ዘንድ አንድ እንግሊዛዊ ካህን ወደ ወኅኒ ቀቱ መጡ፡፡ በስፍራው ዹነበሹ አንድ ዹዓይን ምስክር እንደገለጞው ሁለቱ እስሚኞቜ ያለ ቅጥ እዚተንሰቀሰቁ ሲያለቅሱ ሳሮዊዋ ተመልክቶ ጠጋ በማለት ለእናት ምድራ቞ው ናይጄሪያና ናይጄሪያውያን መሥዋዕት በመሆናቾው ሊኮሩ እንደሚገባ቞ው በመንገር በድፍሚት ዚሞትን ጜዋ ይጠጡ ዘንድ ነበር ያበሚታታ቞ው፡፡
ዚሞት ፍርዳ቞ው በሚጞናበት ሚፋድ ጠዋት ላይ ኬን ሳሮዊዋ አዘውትሮ ኚኚንፈሩ ዚማይነጥላትን ፒፓውን ለአባቱ እንዲሰጡለት ገዳዮቹን ተማጞነ፡፡ ጥያቄውን ዹተቀበለው ሰው ግን አልነበሚም፡፡ ወዲያው ዚአምባገነኖቹ ቅጥሚኛ ዚሆኑት ወታደሮቜ ዚእስሚኞቜን ዓይን በጥቁር ጹሹቅ ሾፍነው ወደ መስቀያው ስፈራ እያጣደፉ ወሰዷ቞ው፡፡ ኬን ሳሮዊዋ ዚመጀመሪያው ተሰቃይ ነበር፡፡ ይሁን እንጂ በሚገርም ሁኔታ በኬን ሳሮዊዋ አንገት ውስጥ ዹተጠለቀው ገመድ ለአራት ጊዜያት ያህልም ቢበጠስም በአምስተኛው ግን እነዛ ጚካኞቜና እብሪተኞቜ ሕይወቱን በስቅላት ኚነፍሱ ነጠሏት፡፡
ግዑዙ ገመድ እንኳን እምቢ ለፍትሕ፣ እምቢ ለእውነት ብሎ በኬን ጎን በቆመበት፣ በመሰኚሚበትና ባመጞበት በዛቜ ቅጜበት አምባገነኖቹ ልባ቞ውም ሆነ ዓይናቾው ታውሮ ይኌን እውነት ለመገንዘብ ሕሊናቾውም አእምሮ቞ውም ጚለመባ቞ዋልና ሊምሩት አልወደዱም፡፡ ወታደሮቹ ለጊዜውም ቢሆን ኹዚህ እኩይ ድርጊታ቞ው፣ በክፉው፣ ሞካራና ጠማማ ጎዳና ላይ ኚመገሥገሥ ዚሚያግዳ቞ው ምንም ምድራዊ ኃይል እንደሌለ ነበር ለናይጄሪያ ሕዝብና ለመላው ዓለም ለማሳዚት ዚሞኚሩት፡፡
ታጋይ፣ ደራሲ፣ ጾሐፊ 
 ዹሆነው ኬን ሳሮዊዋ በናይጄሪያ ደቡብ ምስራቅ ጠሹፍ በኒጀር ወንዝ ዳርቻ ዹሚኖር ዚኢጎኒ ብሔር ተወላጅ ነበር፡፡ በ54 ዓመት ዕድሜው በግፍ በገመድ ተንጠልጥሎ ለሕልፈት ዹበቃው ሳሮዊዋ በተለያዩት ጊዜያት በጋዜጊቜ ላይ ባቀሚባ቞ው መጣጥፎቜ፣ ፖለቲካዊና ማኅበራዊ ዹሰላ ትቜቶቹ፣ በ቎ሌቪዥን ዝግጅቶቹና ዘገባዎቹ በድፍን ናይጄሪያ ኹፍተኛ ተወዳጅነትንና ዝናን ለማትሚፍ ዚቻለ ስመ ገናና ጾሐፊና ገጣሚ ነበር፡፡
‹‹ሶልጀር ቊይ›› ዹተሰኘ ወጥ ዚፈጠራ ሥራው ኚአገሩ አልፎ ኚበሬታን ያተሚፈለትና ተነባቢ ሥራው ለመሆን በቅቶለታልም፡፡ ሳሮዊዋ በኑሮው ዹተደላደለ ቱጃር ለመሰኘት ዚሚቜል፣ ዹግሉ ዹሆነ ፕሬስ መሥርቶ በመንቀሳቀስ ላይ ዹነበሹና ይህ ጎደለው ዚማይባል ሰው ዚሚባል ዓይነት ቢሆንም እንኳን ናይጄሪያና ናይጄሪያውያን ዕጣ ፈንታ በአምባገነኖቹና በጚካኙ ወታደራዊ ኃይሎቜ እጅ መውደቁ እሚፍት ስለነሣው አምባገነኖቜን በብዕሩ አምርሮ ለመዋጋት ተነሣ ጀግና ዚብዕር ሰው ነበር፡፡
ታጋዩና ደራሲው ኬን ኚትውልድ ቀዬው በገፍ ዚሚቀዳው ጥቁር ወርቅ (ዚነዳጅ ዘይት) ዚናይጄሪያ 90 በመቶ ዚገቢ ምንጭ ኹመሆኑም በላይ ለሙስናና ለምዝበራ ለተዘፈቁት ወታደራዊ ገዢዎቜ መንደላቀቂያነት ሲውል ታዝቧል፡፡ ሕዝቡ ይህ ነው በማይባል ድህነትና ጉስቁልና ውስጥ ተዘፍቀው አምባገነኖቹ እንዲህ መቀማጠላቾው ዹሕሊና እሚፍት ዚነሣው ሳሮዊዋ ይህን ግፍ ለመበቀል ነበር ብዕሩን በድፍሚት ያነሣው፡፡ በዚህም አምባገነኖቹንና ሙሰኞቹን ናይጄሪያውያንን ክፉኛ ነበር ያሰጚነቃ቞ው፡፡
ደራሲና ታጋይ ኬን ሳሮዊዋ ሙያውን አክባሪና በሙያው ተደሳቜ እንደነበር ለእንግሊዛዊው ደራሲ ዊሊያም ማድዬ በጻፈው ደብዳቀ እንዲህ በማለት ነበር ማንነቱንና ሥራውን ዚገለጞው፡-
በእጅጉ ዚማኚብሚውንና ዹምወደውን ዚኢጎኒ ሕዝብ እነዚያ አበሳውንና ፍዳውን በሚያስቆጥሩት ፈላጭ ቆራጭ ገዢዎቜን እንዲጋፈጣ቞ው ለማድሚግ ዚሥነ ጜሑፍ ስጊታዬን እንደ ታላቅ መሳሪያ ለመጠቀም በመቻሌ በሕይወቮ ውስጥ ትልቁ ነገር ሆኖ ይመዘገባል፡፡ ብዕሬን ለወገኖቌ አርነት ማዋሌን ያህል ሚያስደስተኝ ነገር ዚለም፡፡ ለወገኔ ዚእኔ ድምፅ፣ ዚእኔ ጩኞት በጣሙን ወሳኝና አስፈላጊ ነበር፡፡
በእጅጉ ዹሚደንቅ ነው!! ፖለቲኚኛ ሆኜ እንዲህ ያለ ነገር ማድሚግ አልቻልኩም፣ በንግዱ ዓለም ተሰማርቌ በነበር ወቅትም አልሳካልኝ ያለ ነገር ነበር፡፡ ብዕር አንስቌ ኚወሚቀት ጋር ማዋኻድ ስጀምር ግን ኚባዱ ነገር ቀላል ሆነ፡፡ አልሳካ፣ ድምፁም አልሰማ ያለው ነፃነትና ዚፍትሕ ድምፅም ኚአጥናፍ እስኚ አጥናፍ በምድሬ በናይጄሪያ ተሰምቶ አምባገነኖቹንና እብሪተኞቜን መግቢያና መውጫ አሳጣ቞ው፣ እሚፍትም ነሣ቞ው፡፡
ብዕር  ፣ ብዕር  ፣ ዚብዕር ኃይል ምንጊዜም ያሞንፋል፡፡ ለእኔ ኹዚህ በላይ ደስታ ዚለም፡፡ በዚህ ወቅት ዹፈለገው ነገር ቢመጣም በቆራጥነት ለመጋፈጥ ተዘጋጅቌያለኹ፡፡ እንደሚመስለኝ በዚህ ሰዓት ታላቅ ዹሆነ ዚሞራል ድል ዚተጎናጞፍኩት እኔ ነኝ፡፡ በጠላትነት ዚተነሡብኝ አምባገነኖቜ፣ ጠላቶቌ ኹዘላለማዊ እፍሚትና ጞጞት ኚማያመልጡበት ዚሲኊል ቅርቃር ውስጥ እንደገቡ ሆነው ነው ዚሚሰማኝ፡፡ ነበር ያለው ያ ጀግና ዚብዕር ሰው!!
በእያንዳንዱ ናይጄሪያዊ ሕዝብ፣ ዚአርነት ታጋዮቜና በዓለም ሕዝቊቜ ሁሉ ዘንድ ብሎም ዚኪነ ጥበብ ወዳጆቜና አፍቃሪዎቜ ልብ ውስጥ ኬን ሳሮዊዋ ዛሬም ነገም ሕያው ሆኖ ይኖራል፡፡ አባቻና መሰል አምባገነኖቜ ግን በአሚመኔያዊ ግብራ቞ው ታሪክ በትዝብት ሲያስታውሳ቞ው ይኖራሉ፡፡
በመጚሚሻም በአገራቜን ታላቅ ዹሆነ ብዕራዊ ተጋድሎ ያደሚጉትን እነ ጞጋዬ ገ/መድኅንን፣ እነ አቀ ጉበኛን፣ እነ በዓሉ ግርማን አርአያ አድርገው ዛሬም ስለ እውነት፣ ስለ ፍትሕ፣ ስለ ነፃነት 
 በጚዋ፣ በታሚመና ባላመነዘሚ ብዕራ቞ው ተጋድሎ እያደሚጉ ላሉ ኢትዮጵውያን ሁሉ ያለኝን አድናቆትና ክብር ለመግለጜ እወዳለኹ፡፡
በአቀ ጉበኛና በበዓሉ ግርማ መንፈስ፣ ሌሎቜም በዚህ ዘመን ዚእነርሱን ብዕር ቁርጠኝነትና ወኔ ዹተቀላቀሉ ኃያላንና ጀግኖቜ ብዕሚኞቜ ለተገፉ ወገኖቻ቞ው፣ ለሰው ልጆቜ መብት፣ ለፍትሕና ለእውነት በመቆም በተባ ብዕራ቞ው ላደሚጉትና እያደሚጉት ላለው ታላቅ ተጋድሎ ሊዘኚሩ ዚሚገባ቞ው ዹምን ጊዜም ዚኢትዮጵያ ዚብዕር ጀግኖቻቜን ናቾውና ልናኚብራ቞ው፣ ልንዘክራ቞ው ይገባናል ለማለት እወዳለኹ፡፡
ሰላም! ሻሎም!

↧

ዚኢሕአግ ሰራዊት በዋልድባ ወታደራዊ ጥቃት መፈጾሙን አስታወቀ

0
0

eppfዚኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞቜ ግንባር ሰራዊት በዋልድባ አካባቢ ልዩ ስሙ ሰቋር እና አምቩ ጠበል በተባለ ቊታ በተኚታታይ ሁለት ቀናት ኚወያኔው ዚፈጥኖ ደራሜ ጋር ባደሚገው ዚፊት ለፊት ውጊያ በጠላት ላይ ወታደራዊ ዚበላይነትን በመቀዳጀት አኩሪ ዚአርበኝነት ጀብድ ፈጞምኩ ሲል ለዘ-ሐበሻ በላኹው ጋዜጣዊ መግለጫ አስታወቀ።

ዚድርጅቱ ጋዜጣዉ መግለጫ “ ዚግንባሩ ሰራዊት በዋልድባ ልዩ ስሙ ሰቋር በተባለ ቊታ በሚያዚያ 8-2005 ዓ.ም ዚወያኔ አምባገነናዊ አገዛዝ መመኪያ በሆነው ዚፈጥኖ ደራሜ ላይ በኹፈተው ዚማጥቃት እርምጃ 21 ዚጠላት ወታደሮቜን በመግደል 25 አቁስያለሁ” ካለ በኋላ በተመሳሳይ በሚያዚያ 9-2005 ዓ.ም በዋልድባ ልዩ ስሙ አምቩ ጠበል በተባለው ቊታ ውጊያ መካሄዱንና  በዚሁ እለትም ዚኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞቜ ግንባር ሰራዊት 25 ዚወታደሮቜን ገድሎ 39 በማቁሰል ኹፍተኛ ድል ዚተቀዳጀ መቀዳጀቱን ጠቅሶ  በዚሁ አውደ-ውጊያ ላይም ዚተለያዩ ዚቡድንና ዚነፍስ ወኹፍ ዹጩር መሳሪያዎቜንም ኹመሰል ጥይቶቻ቞ው ጋር መማሚኩን አትቷል።

“ዚኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞቜ ግንባር ሰራዊት በሁለት ተኚታታይ ቀናት ባደሚጋ቞ው አውደ-ውጊያዎቜ ላይ በድምሩ 46 ዚፈጥኖ ደራሟቜን ኚጥቅም ውጭ በማድሚግና 64 በማቁሰል ዚግንባሩ ሰራዊት ዚተሰለፈበትን ሐገራዊ ተልዕኮውን በመፈፀም በጠላት ላይ ኹፍተኛ ዚሕይወትና ዚንብሚት ኪሳራ በማድሚስ አኩሪ ዚአርበኝነት ጀብድ ፈፅሟል።” ያለው ዚድርጅቱ መግለጫ “ ዚግንባሩ ሰራዊት ጥቃቱን በፈፀመበት አካባቢ ዚሚኖሩ ዚሕብሚተሰብ ክፍሎቜም ስርዓቱ በሚያራምደው ዹግፍ አገዛዝ ኹፍተኛ ምሬትና ተቃውሞ በማሰማት ዚኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞቜ ግንባር ሰራዊትም ዹጀመሹውን ወታደራዊ ዚማጥቃት እርምጃ አጠናክሮ እንዲቀጥል ዚበኩላ቞ውን አስተዋፅዖ በማበርኚት ሐገራዊ ግዎታ቞ውን ለመወጣት ወደ ግንባሩ ሰራዊት እዚተቀላቀሉ ይገኛሉ” ሲል ጋዜጣዊ መግለጫውን አጠናቋል።

ዚአርበኞቜ ግንባር በበተነው ጋዜጣዊ መግለጫ ዙሪያ ዚኢሕአዎግ መንግስት ዹሚሰጠውን ምላሜ ለማካተት ያደርገነው ጥሚት ባይሳካምፀ እስካሁን በይፋ ዹሰጠው ምላሜም ዚለም።

↧

ወደ ቀንሻንጉል ዚተመለሱት አማሮቜ ዚተሰጣ቞ው ዱቄት ወሚርሺኝ እያመጣባ቞ው ነው

0
0

New Picture (5) ኚቀንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ተባሚው ወደ ፍኖተ ሰላም ኚተማፀ ኹፍኖተ ሰላም ኹተማ ደግሞ እንደገና ወደ መጡበት በግዳጅ እንዲመለሱ ዚተደሚጉት ዚአማራ ተወላጆቜ በርሃብ እዚተቀጡ መሆኑን ኢሳት ራድዮ ዛሬ በስፍራው ያሉትን በማነጋገር ዘገበ። ለምግብነት ዚተሰጣ቞ው ዱቄት ወሚርሺኝ እንዳመጣባ቞ው ያጋለጠው ዚኢሳት ዘገባ በቀንሻንጉል ጉምዝ ግዙፍ ዚሰብአዊ መብት ጥሰት እዚተፈጞመ ነው ይላል። ያድምጡት።

↧

ትዳር ለምን ሰላም አልባ ይሆናል? መፍትሄውስ 

0
0

51197D367BA550D871870C1D732FA_h296_w526_m2_bblack_q100_p100_cLzUgTDNf

በእውነተኛ ፍቅር ውስጥ መሆንዎን ማወቅ ይፈልጋሉ?

ኹሊሊ ሞገስ

‹‹ጋብቻ ክቡር ነው መኝታውም ቅዱስ ነው››
ሰዎቜ በህይወት ዘመናቾው ውስጥ ማኹናወን ኚሚገባ቞ው ነገሮቜ ውስጥ አንዱ እና አብይ ዹሆነው ጋብቻ ነው፡፡ ለዚህም ይመስላል ብዙ ቁጥር ያላ቞ው ሙሜሮቜን ዚምንመለኚተው፡፡ ይሁን እንጂ በተመሳሳይ መልኩ ባማሚና በደመቀ ስነ ስርዓት ባይሆንም፣ በቁጥር /በብዛት/ ዹበለጠው ቡድን ኹፍተኛ ዹሆነ ሜልማት ያገኛል ዚተባለ ይመስላል ክቡር ዹሆነውን ጋብቻ ሹግጠውና ጥለው ትስስራ቞ውን ለመበጣጠስ ዚዚፍርድ ቀቱን ቜሎት ዚሚያጚናንቁ ባለትዳሮቜ ቁጥር እጅግ ኹፍተኛ ሲሆን በሌላ በኩል ዚፈጠሩት ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ትስስር ሚዛኑን ደፍቶ መፍታት ሳይቜሉ በመካኚላ቞ው ሰላም፣ ፍቅርና ደስታ ጠፍቶ እንዲያው ለይስሙላ አብሚው ዚሚኖሩት ቁጥር ደግሞ ኚተፋቱት ዹሚበልጠው ነው፡፡ ይህንንም ዚሚያሚጋግጠው ጥናታዊ መግለጫ ነው፡፡
ባለፉት አስር ዓመታት ውስጥ ኚተመሰሚቱ ትዳሮቜ 1/3ኛው በጥንዶቜ መካኚል እውነተኛ ፍቅር ሰላምና ደስታ በመጥፋቱ ትዳር በፍቺ ሊቋጭ ቜሏል በማለት ሰሞኑን ዹገለፀው በተለያዩ ዚዓለማቜን ክፍል በጋብቻ ዙሪያ ጥናት ዚሚያደርግ አንድ ዚተመራማሪዎቜ ቡድን ሲሆን፣ በተመሳሳይ ወቅት በዚሁ ጉዳይ /በጋብቻ/ ዙሪያ ዚሚያጠና ቡድን ኚስድስት ጥንዶቜ /ባለትዳሮቜ/ መካኚል ደስተኛና ሰላማዊ በመሆን ዚትዳር ህይወታ቞ውን ማስቀጠል ዚቻሉት /ዚቻለው አንዱ ትዳር መሆኑን ማሚጋገጥ ቜያለሁ ብሏል፡፡
እንግዲህ ይህ በገሀዱ ዓለም ዚሚታዚው እውነታ ለሁሉም ባይሆንም ለብዙዎቜ ዚጋብቻቜን ክቡርነት ዚመኝታውም ቅዱስነት ማርኚስ ማለት አይደለም ትላላቜሁ?
ይሁን እንጂ ዚጋብቻን ክቡርነት ዚመኝታውንም ቅዱስነት ጠብቆ መጓዝ ዚጥንዶቹ ዚውዎታ ግዎታ መሆን ይኖርበታል፡፡ ይህንን ግዎታ ለመወጣት ደግሞ ሰው ሆነን በመፈጠራቜን ዹተሰጠን ትልቅ ብቃትና ፀጋ አለን፡፡ ነገር ግን ይህን ብቃታቜን ተጠቅመን በጋብቻ ውስጥ መኖር ያለበትን ሰላም፣ ፍቅርና ደስታ እያጣጣምን ለመኖር ስላለንበት ዘመን እውነታ፣ ስለ እውነተኛ ፍቅር ምንነት እና ስለ ትዳር ጠንቅቀን ማወቅ ግድ ይለናል፡፡ ለዛሬ በዚህ ዙሪያ ጥቂት ለማለት ወደድን፡፡
መልካም ንባብ

በእርግጥም ሁሉም ጥንዶቜ /ተጋቢዎቜ/ በወግ በማዕሹግ ተውበውና ተሞሜሚው በደመቀ ዹሠርግ ስነ ስርዓት ትዳራ቞ውን መመስሚት መፈለጋቾው ዚማይታበል ሀቅ ነው፡፡ በመሆኑም ሁሉም እንደዚአቅሙ ወይም እንደ ገቢ መጠኑ ወይም እንደዚአስተሳሰቡ ኚእወቁልኝ ካርድ እና በጣት ዚሚቆጠሩ ታዳሚዎቜ ኚማሳተፍ ጀምሮ አገር ጉድ ዚሚያሰኝ ድል ያለ ሠርግ በመሰሹግ ዚትዳር ህይወቱን አንድ ብሎ ይጀምራል፡፡ ይሁን እንጂ እዚህ ጋር ልብ ሊባል ዚሚገባው ትልቁ ነገር ዚትኛውም አይነት ዹሠርግ ስነ ስርዓት በተጋቢዎቜ መካኚል ዘላቂነት ያለው እርካታና ዚደስተኝነት ስሜት ለማምጣት ምንም አይነት አስተዋፅኊ እንደሌለው ወይም ለዘላቂ ደስተኝነታ቞ው ዋስትና ሊሆን እንደማይቜል ነው፡፡ እንዲያውም አንዳንድ ኹፍተኛ ዚገንዘብ ወጪ ዚተደሚገባ቞ውና ብዙ ዚተደኚመባ቞ው ሠርጎቜ ተጋቢዎቹ /ጥንዶቹ/ ዚሜርሜር ጊዜያ቞ውን ሀኒሙኒያ቞ውን ሳይጚርሱ በመካኚላ቞ው ሰላምና ደስታ እዚራቀ ሲሄድ ይስተዋላል፡፡
ምንም እንኳ እውነታው ይህ ቢሆንም፣ ማንኛውም ትዳር ዘላቂነት ያለው ደስታ፣ ፍቅርና ሰላምን በውስጡ እንደያዘ ለሁልጊዜም መጓዝ ይቜላል ዚሚሉት ዹዘርፉ ተመራማሪ ሊቃውንቶቜ፣ ይህ ሊሆን ዚሚቜለው ግን ጥንዶቹ በተናጥልም ሆነ በጋራ ለትዳራ቞ው ዚጋራ ጥቅም በእውነተኛ ስሜትና ፍላጎት ሲያስቡና ሲሰሩ ነው ይላሉ፡፡ አክለውም ነገር ግን እዚህ ጋር ሊሰመርበት ዚሚገባው ጉዳይ ጥንዶቜ ወደ ትዳር ህይወት ኚመግባታ቞ው በፊት አንድ አስደሳቜ እና ማራኪ ትዳር ለመመስሚት ዹሚጠይቀውን መስፈርት አስቀድመው ማሟላት ዚቻሉ እንደሆነ ነው ብለዋል፡፡
በእርግጥ በባለ ትዳሮቜ መካኚል ዘላቂነት ያለው አስደሳቜና ሰላማዊ ዚትዳር ህይወትን ሊያስገኝ ወይም ሊያመጣ ዚሚቜል አንድ አይነት ዚሂሳብ ቀመር ወይም መመሪያ ባይገኝም፣ ምናልባት በእውነታው ዓለም ውስጥ ያለ ዚዚራስ መሻታ቞ውን ለማርካት ትዳሩ ኹፍተኛ አስተዋፅኊ ካበሚኚተ በጥንዶቹ መካኚል ቀጣይነት ያለው ደስተኝነትና ፍቅር ሊኖር ይቜላል፡፡ ይህን እንደ መመሪያ ወይም ቀመር መውሰድ ሁላቜንንም ሊያስማማ ይቜላል፡፡ ማለትም አንድ ሰው በትዳሩ ወይም በትዳር አጋሩ ደስተኛ መሆን ዚሚቜለው በትዳሩ ውስጥ ዚኑሮ እና ዚአጋርነት ዋስትና ዚማግኘት ፍላጎቱ፣ ዹሁልጊዜ ተወዳጅና ተፈቃሪ ዹመሆን ፍላጎቱ፣ በተጓዳኙ ዘንድ አስፈላጊና ጠቃሚ ሰው ስለመሆኑ እውቅና ዚማግኘት ፍላጎቱ /recognition/ እና ሌሎቜ መሰሚታዊ ፍላጎቶቹ ሁሌም መርካት ዚቻሉ እንደሆነ ነው፡፡ ይሁን እንጂ እነዚህ ፍላጎቶቜን ማሟላት በራሱ ፈታኝ መሆኑ እንዳለ ሆኖ እነዚህ ፍላጎቶቜ በተሟሉበት ሁኔታ ውስጥ በባለ ትዳሮቜ ሰላማዊና አስደሳቜ ዹፍቅር ሕይወት ላይ ጥላውን ዚሚያጠላው አሁን ዚሚታዚው ዘመናዊ አኗኗር /Modern living/ ዹፈጠሹው ቜግር መሆኑ ይታመናል፡፡
ማለትም ዘመኑ በወለደው ዘመናዊ አኗኗር ውስጥ ዹተፈጠሹው ያልተሚጋጋ ኢኮኖሚ /ዚገቢና ወጪ አለመመጣጠን/ ኹፍተኛ ውጥሚትና ጭንቀት፣ ዹጊዜ እጥሚት፣ ዹሰላም መጥፋት፣ ኹፍተኛ ዚጥሎ ማለፍ ውድድርና ሌሎቜ ለዘመናቜን ባለትዳሮቜ አስደሳቜ ዚትዳር ህይወት መጥፎ መሰናክል እንደሆኑ ይታመናል፡፡
ይሁን እንጂ እነዚህ አስ቞ጋሪ ሁኔታዎቜ ወይም መሰናክሎቜ ለዘመናቜን ባለትዳሮቜ ፈታኝ መሆናቾው ዚማይታበል ሀቅ ቢሆንም ማንኛውም ሰው በዹዘመኑ ዚሚያጋጥሙትን አስ቞ጋሪና ፈታኝ ሁኔታዎቜ በጣጥሶ በድል በማለፍ ካሰበውና ካለመው ለመድሚስ ዚሚስቜል ተፈጥሯዊ ብቃት ባለቀት ስለመሆኑ ዚቀደሙትም ሆኑ ዚዘመናቜን ስኬታማ ባለትዳሮቜ ህያው ምስክሮቜ ና቞ው፡፡ በመሆኑም ወጣቶቜ ዹግልም ሆነ ዚጋራ ፍላጎታ቞ውን ዚማሳካት ጜኑ እምነትና ዚተቀራሚበ ስብዕና ወይም ስነ ልቩና ባለቀት ኹሆኑ ዘላቂ ደስታ፣ ፍቅርና ሰላም ዚሰፈነበት ዚትዳር ህይወት መምራት እንደሚቜሉ በእርግጠኝነት መናገር ይቻላል፡፡
እንግዲህ ስለ ትዳር ወይም ጋብቻ ስናነሳ በጥንዶቹ መካኚል ዹሚፈጠሹው ፍቅር መሰሚታዊና ቀዳሚ ጉዳይ ስለመሆኑ ምንም ጥርጥር ዚለውም፡፡ በመሆኑም በአጠቃላይ ስለ ፍቅር ወይም ስለ ፍቅር ትርጓሜ ኚተለያዩ አቅጣጫዎቜ ለማዚት እንሞክር፡፡

ፍቅር
ፍቅር ማለት አንድ ሰው ኹሌላ ሰው ጋር ጠንካራና ዹጠበቀ ዹግል ግንኙነት እንዲኖሚው እና ያፈቀሚውን ሰው ደስታና ደህንነት እንዲሁም ሌሎቜ ፍላጎቶቜ ዚማሟላት ብሎም ዹበለጠ ዚማሳደግ ኹፍተኛ ፍላጎትና ኃላፊነት እንዲያድርበት ዚሚስቜል እውነተኛ ስሜት ማለት ነው፡፡ በፍቅር ውስጥ ያለ ሰው ዚውዎታ ደሚጃው፣ ዹጠለቀ ፍላጎት፣ ዚተቆርቋሪነት ስሜት እና ሌሎቹ መልካም ፍላጎቶቜን በዹጊዜው እዚገነባ እና እያዳበሚ ይሄዳል፡፡
ፍቅር ማለት ያፈቀሩትን ሰው መርዳት ወይም ማወቅ ማለት ነው፡፡ ኹጠለቀ እውቀት፣ ኚአስተዋይነት እይታ እና ኚዳበሚ ልምድ ዹፈለቀ ጥልቅ መሚዳት፡፡ ያፈቀሩትን ሰው መሚዳት ወይም ጠንቅቆ ማወቅ ማለት ስለ ግለሰቡ ስሜት፣ ፍላጎት፣ ባህሪ፣ ጉድለትና ሌሎቜ በቂ እውቀት ማግኘት ማለት ነው፡፡
ስላፈቀሚው ሰው በቂ መሚዳት ያለው አፍቃሪ፣ ያፈቀሚውን ሰው ስሜት ዚሚጎዳ ድርጊት ዹመፈፀም አጋጣሚም ሆነ ዚሚያስቀይም ቃል ዹመናገር እድል አይኖሚውም፡፡ በመሆኑም በእውነተኛ ፍቅር ውስጥ ባሉ ጥንዶቜ መካኚል ዹሚኖሹው አለመግባባት /misunderstanding/ አነስተኛ ወይም ኚቁጥር ዚማይገባ መሆን ይቜላል፡፡
ፍቅር ማለት እምነት ወይም መተማመን ማለት ነው፡፡ ፍቅር ማለት ፍቅሚኛሞቜ እርስ በእርሳ቞ው በሚኖራ቞ው ውህደት ወይም ቁርኝት፣ ታማኝነት እና ፍትሀዊነት ወይም ሚዛናዊነት ላይ እርግጠኝነት እንዲሰማ቞ው ዚሚያደርግ እምነት ወይም መተመመን ማለት ነው፡፡ ይህም አፍቃሪው ለተፈቃሪው ዚገባውን ቃል አክባሪነቱንና ታማኝነቱን ስለሚያሚጋግጥ ተፈቃሪው በአፍቃሪው ላይ ሙሉ እምነትና መተማመን እንዲያሳድር ኚማድሚጉም ባሻገር ዚራሱንም ታማኝነትና እውነተኝነት ጠብቆ እንዲዘልቅ ያስገድደዋል፡፡ በዚህም ተፈቃሪዎቜ ሙሉ እና እውነተኛ ዚርስ በርስ መተማመን መፍጠር ይቜላሉ፡፡
ፍቅር ማለት አንደኛው ለሌላኛው ቅድሚያ ዚሚሰጥበት እና አንድነትን በመፍጠር ወገናዊነቱን ዚሚያሳይበት መድሚክ ነው፡፡ ያፈቀሩትን ሰው መሻትና ፍላጎት እውን ይሆን ዘንድ ዚራስን /ዹግልን/ ፍላጎት፣ ደስታና ስሜት አሳልፎ መስጠት ወይም መስዋዕት ማድሚግ ጎልቶ ዚሚታይበት መድሚክ ነው፡፡ ይህ መድሚክም ተፈቃሪው ዚራሱን ስሜትና ፍላጎት ለአፍቃሪው አሳልፎ ዚመስጠት ዝንባሌና ፍላጎት እንዲያድርበት ያደርጋል፡፡ በዚህም ለተፈቃሪዎቜ ዹዹግል ፍላጎትና መሻታ቞ውን አንደኛው ለሌላኛቾው አሳልፈው ለመስጠት ወይም መስዋዕት ለማድሚግ ፈቃደኝነት እና ዝግጁነት እንዲኖራ቞ው ማድሚግ ያስቜላል፡፡ እንግዲህ ይህ ደሹጃ በደሹጃ በጥንዶቜ መካኚል ዹሚፈጠሹው ህብሚት ወይም አንድነት ዚሚገለፅበት ዹላይኛው እርኚን ነው፡፡
ፍቅር ማለት በትልቅ ስሜት መዋደድ ወይም ዹፍቅርን ስሜት በተዋበና ባማሚ መልኩ መግለፅ ማለት ነው፡፡ ዹፍቅር ስሜትን ወይም በግንኙነት ዹሚፈጠር ደስታና እርካታና ላፈቀሩት ሰው ዚሚገልፁበት ማራኪና ቀልብ ገዢ ድርጊታዊ እንቅስቃሎ ወይም አርት ማለት ነው፡፡
አፍቃሪው ኚተፈቃሪው ሰው ጋር ሲገናኝ ዚሚተቃቀፍበት አስተቃቀፍ ዹወደደውንና ዹተመኘውን ገላ ዚሚደባብስበት አደባበስ፣ አብሚው ዚእግር ጉዞ ሲያደርጉ /ሲንሞራሞሩ/ እጆቿን/ቹን ዚማይዝበት/ዚምትይዝበት አያያዝ፣ ወገቧን/ወገቡን ዚሚያቅፍበት/ዚምታቅፍበት አስተቃቀፍ፣ ኹንፈር ለኹንፈር ዚሚሳሳሙበት አሳሳም በቃ ምን አለፋቜሁ አጠቃላይ እንቅስቃሎና ድርጊቱ/ቷ ውበትና አርት ዹተላበሰ መሆኑ ዚተፈቃሪውን ልብ በሀሎት ጮቀ ኚማስሚገጡ ባሻገር ተመሳሳይ ወይም ዹበለጠ ምላሜን እንዲሰጥ ያደርገዋል፡፡ እንግዲህ ይህ ሁኔታ በፍቅሚኛሞቜ መካኚል ያለውን ጥልቅ ፍቅር በተለዹ መልኩ ማስኬድ ዚሚቻልበት ሂደት ነው፡፡
እንግዲህ በፍቅሚኛሞቜ መካኚል ዹሚፈጠሹው እውነተኛ ፍቅር ማለት ኹላይ እንዳዚነው ሲሆን፣ ለትዳር ህይወት መቀዝቀዝ ምክንያት ዹሚሆኑ ተጚማሪ ነገሮቜን ለማዚት እንሞክር፡፡ ፍቅሚኛሞቜ ደስተኛና ስኬታማ ዚትዳር ህይወት ለመምራት ሁለቱም ግለሰቊቜ በዹግላቾው ፍቅር መስጠትና መቀበል ወይም ኹላይ ዚተገለጡትን መግለጫዎቜ መተግበር ይኖርባ቞ዋል፡፡ አለበለዚያ በአንድ ወገን ብቻ ዹሚደሹግ ጥሚት/ፍቅር መስጠት ውጀታማ ሊሆን አይቜልም፡፡ ማለትም አልፎ አልፎ አንዳንድ ተፈቃሪዎቜ ፍቅርን ዚመስጠት ብቃታ቞ው ወይም ስሜታ቞ው በእጅጉ ዚተጎዳ ዚሚሆኑበት አጋጣሚ አለ፡፡ ምናልባትም በአስተዳደጋ቞ው ወይም በሆነ ወቅት ዚደሚሰባ቞ው በደል እንደ አስገድዶ መድፈር ያለ መጥፎ ጠባሳ ወይም በሌላ ተመሳሳይ ምክንያት ዚተፈጠሚባ቞ው ቜግር ሊሆን ይቜላል፡፡ በመሆኑም እነዚህ ሰዎቜ ፍቅርን መስጠት እና መቀበል በተለይም ፍቅር ዚመስጠት/ዹፍቅር ስሜታ቞ውን መግለፅ ብቃትና ቜሎታ቞ውን መልሰው ማምጣት ዚሚቜሉበትን ዚስነ ልቩና ህክምና ኚማግኘታ቞ው በፊት ወደ ትዳር ህይወት መግባት እንደሌለባ቞ው ይመክራል፡፡ ምክንያቱም ስኬታማ ዚትዳር ህይወትን ለመምራት ፍቅርን መስጠትና መቀበል ወይም ሌላውን ዹማፍቅር ፍላጎት መሰሚታዊ በመሆኑ ነው፡፡
ሌላው ለትዳር መፍሚስ ወይም ደስተኛ ዚትዳር ህይወት ላለመምራት ተጠቃሜ ምክንያት ዹሚሆነው ተፈቃሪዎቜ ወደ ትዳር ኚመግባታ቞ው በፊት ዚሚመሰርቱት ፍቅር እውነተኛ ወይም ፍቅር ዚሚመስል ነገር ፍቅር ያልሆነ ጊዜያዊ ስሜት (infatuation) መሆን አለመሆኑ ለይተው ላያውቁ ወይም እውነተኛ ፍቅር መስሏ቞ው መጀመራ቞ው ነው፡፡ በእርግጥ አንድ በፍቅር ስሜት ውስጥ ያለ ‹‹ያፈቀሚ ሰው›› ዚያዘው ፍቅር ኚእውነተኛ ስሜት ዹመነጹ ፍቅር ይሁን ኹተመለኹተው አካላዊ ቁመና ወይም ኚተፈጠሚበት ዚወሲብ ስሜት ዹመነጹ ዹፍቅር ስሜት ይሁን በቀላሉ ለመለዚት ያዳግተዋል፡፡ ይሁን እንጂ እውነተኛ ፍቅር ማለት ኹላይ ለማዚት እንደሞኚርነው፣ ያፈቀሩትን ሰው ዚማወቅ፣ ዚመተማመን፣ ዚመተባበር ወይም አንድነትን ዹመፍጠርና ሌሎቜ እውነታዎቜ በውስጡ ዚያዘና ጊዜ ዹሚጠይቅ ነው፡፡ በመሆኑም እውነተኛ ፍቅር ሹዘም ያለ ጊዜ ዹሚጠይቅ እንጂ በአንድ ቀን ወይም ሳምንት ወይም ወር ውስጥ ዹሚፈጠር አይደለም፡፡ በአይናቜን አይተን ስለተማሚክን ወይም በወሲብ ስሜት (መሻት) ዹሚፈጠር ፍቅር ብዙ ጊዜ ፍቅር ዚሚመስል ጊዜያዊ ስሜት ሲሆን ተፈቃሪዎቜ ወደ ትዳር ካመሩ አልፎ አልፎ ግንኙነታ቞ው ወደ እውነተኛ ፍቅር ዹመሾጋገር እድል ቢኖሚውም በአብዛኛው ግን በሰላም እና ደስታ ማጣት ብሎም በመለያዚት (በፍቺ) ዹሚደመደም ይሆናል፣ እንዲሁም ወሲብን (ኚወሲብ መጣጣምና እርካታን) ብቻ መሰሚት በማድሚግ ዚሚመሰሚት ጋብቻም ተመሳሳይ እጣ ፈንታ እንደሚኖሚው ይታመናል፡፡
በአጠቃላይ ለአንድ ትዳር ዘላቂ ሰላም፣ ደስታ እና እርካታ ዹጎላ ድርሻ ያለውን እውነተኛ ፍቅር ሁሉም እንዲኖሚው ዚሚመኘው፣ ነገር ግን ጥቂቶቜ ብቻ ዚሚያጣጥሙት ቢሆንም ሀቁ ይህ ሊሆን ዚቻለው ኚራሳቜን ድክመት እንጂ ኚእውነተኛ ፍቅር ባህሪ እና መገለጫ ወይም ተአምራዊነት አለመሆኑን ሁላቜንም አምነን ልንቀበለው ይገባል፡፡ እንዲያውም ማወቅና መገንዘብ ዚሚገባን እውነተኛ ፍቅር ማለት ለሁሉም ዹሰው ልጅ ዹተሰጠ ተፈጥሯዊ ፀጋ እና በጊዜ ሂደት ውስጥ በቀላሉ ማግኘት ዚሚቻል ቅዱስ ነገር እንደሆነ ነው፡፡

በእውነተኛ ፍቅር ውስጥ መሆን አለመሆንዎን ማወቅ ይፈልጋሉ?
እንግዲያውስ ኚታቜ ዚተዘሚዘሩትን ጥያቄዎቜ በጥንቃቄ መርምሹው ይመልሱ

ኚፍቅሚኛዎት ወይም ኚትዳር አጋርዎት ጋር አንድ ላይ በሚሆኑበት ወቅት ወይም በሆነ ርዕስ በሚነጋገሩበት ወቅት ወይም ዹሆነ ስራ በጋራ በሚያኚናውኑበት ወቅት ዚደስታ ስሜት ይሰማዎታል?

ኹፍቅሹኛዎ ወይም ኚትዳር አጋርዎ ጋር ሹዘም ላለ ሰዓት በሆነ ጉዳይ በሚወያዩበት ወቅት እርስ በርስ ኚመሰለቻ቞ት ውጭ መሆን ይቜላሉ? መሰሚታዊ ፍላጎቶቻቜሁ በተቀራራቢ ወይም በተመሳሳይ ነገሮቜ ላይ ነው? ብዙ ጊዜ ተመሳሳይ ወይም ተቀራራቢ ሀሳቊቜ /እና አላማዎቜ ይኖራቜኋል? እርስ በርስ በጥልቀትና በእርግጠኝነት እንተዋወቃለንፀ ወይም ፍቅሚኛዬን አውቀዋለሁ እሚዳዋለሁ ይላሉ?

ኚትዳር አጋርዎ ዚያዞት ፍቅር ኚማንነታ቞ው እንጂ ኹላይ ካዩት አካላዊ ውበት ወይም ካገኙት ወሲባዊ እርካታ ስላለመሆኑ እርግጠኛ ነዎት?

አልፎ አልፎ ለሚያጋጥማቜሁ ዚሀሳብ ልዩነቶቜ እና አለመግባባቶቜ መፍትሄ ለመስጠት ወይም ወደ ጋራ ስምምነት ለመምጣት ተስማሚ /ተደራዳሪ/ ይሆናል?

አልፎ አልፎ ዚሚፈጠሩ ንትርክና ጭቅጭቆቜ ዚተሻለ መፍትሄ በማግኘት ይቋጫሉ?

አንድ ነገር ሲያስቡም ሆነ ሲያቅዱ እኔ በሚል ሳይሆን /እኔና ፍቅሚኛዬ/ በሚል ስሜትና መንፈስ ነው?

ፍቅሹኛዎን ወይም ዚትዳር አጋርዎን ሁሌም ለማስደሰት ይሞክራሉ?

ሰዎቜ በሚሰበሰቡበት ስፍራ ኹፍቅሹኛዎ ወይም ኚትዳር አጋርዎ ጋር ሆነው መታዚትዎ ዚኩራትና ዚደስታ ስሜት ይፈጥርቊታል?

በመካኚላቜሁ ያለውን ግንኙነት ዹበለጠ ለማሳደግ ዚተለያዩ ጥናቶቜን በማካሄድ ለተግባራዊነቱ በሙሉ አቅምዎ ይጥራሉ?

ልብ ይበሉ፡-
ኹላይ ለተዘሚዘሩት ጥያቄዎቜ መልስዎ ‹‹አዎ›› በትክክል ዹሚል ኹሆነ በእውነተኛ ፍቅር ውስጥ ለመሆንዎ ምክንያታዊ ማሚጋገጫ አገኙ ማለት ነው፡፡
መልካም ዚትዳር ህይወት

↧
↧

ዚኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ “መንግስት ለኔና ለቀተሰቀ ጥበቃ ያድርግልኝ”ሲሉ ተማጾኑ

0
0

sewenet Bishaw
ኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ዋና አሰልጣኝ ሠውነት ቢሻው ዹተወሰኑ ዚኢትዮጵያ ቡና ደጋፊዎቜ በተለያዩ ጊዜዎቜ እያደሚሱባ቞ው ዹሚገኘው ጫና ሥራ቞ውን በአግባቡ ለማኹናወን እንዳይቜሉ እንዳደሚጋ቞ው በመግለጜ ጫናው በእርሳ቞ውና በቀተሰባ቞ው ላይ ጉዳት ይደርሳል ዹሚል ስጋት ስለፈጠሚባ቞ው « መንግሥት ጥበቃ ያድርግልኝ » ሲሉ መጠዹቃቾውን መንግስታዊ ሚዲያዎቜ ዛሬ ዘገቡ።
አሰልጣኙ ለኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዎሬሜን በጻፉትና ለመንግሥት ኮሙኒኬሜን ጉዳዮቜ ፣ ለፌዎራልና ለአዲስ አበባ ፖሊስ ፣ለስፖርት ኮሚሜን ፣ ለኢትዮጵያ ቡና ስፖርት ክለብ እንዲሁም ለመንግሥትና ለግል ዹመገናኛ ብዙኃን በግልባጭ ባሳወቁት ደብዳቀያ቞ው ላይ እንደገለጹት ዹተለመደ ስራ቞ውን ለማኹናወን ስ቎ዲዚም በሚገኙባ቞ው አጋጣሚዎቜ ኹተወሰኑ ዚኢትዮጵያ ቡና ደጋፊዎቜ እዚደሚሰባ቞ው ዹሚገኘው ኚስፖርቱ ስነ ምግባር ውጪ ዹሆነ ድርጊት በስራ቞ው ላይ ጫና ፈጥሮባ቞ዋል። ይህ ድርጊት በእርሳ቞ውና በቀተሰባ቞ው ላይ አደጋ ሊፈጠር ይቜላል ዹሚል ስጋት ስለፈጠሚባ቞ው መንግሥት ጥበቃ እንዲያደርግላ቞ው ለመጠዹቅ አስገድዷ቞ዋል።
አሰልጣኝ ሰውነት በፊርማቾው አስደግፈው በላኩት መግለጫ ፀ እነኝህ «ዚተወሰኑ » ሲሉ ዚገለጿ቞ው ዚኢትዮጵያ ቡና ደጋፊዎቜ ዚካቲት 26 ቀን 2005ዓ.ም ብሔራዊ ቡድኑ ለአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ኚቀኒን አቻው ጋር በአዲስ አበባ ስ቎ዲዚም በተጫወተበት ወቅት ዚእርሳ቞ውንና ዚቡድኑን ተጫዋ቟ቜ ስብዕና ዚሚነካ ስድብና ዘለፋ በመሰንዘራ቞ው ተጫዋ቟ቻ቞ው ውጀት እንዳያስመዘግቡ እንቅፋት ሆነዋል ብለዋል።
በተመሳሳይ መጋቢት 15 ቀን 2005ዓ.ም ብሔራዊ ቡድኑ ኚቊትስዋና አቻው ጋር በአዲስ አበባ ስ቎ዲዚም ባደሚገው ዹዓለም ዋንጫ ማጣሪያ ጚዋታ እነዚሁ ደጋፊዎቜ « ሠውነት ዚኢትዮጵያ እግር ኳስ ገዳይፀ ሠውነት ጋዳፊ » እያሉ ዚስራ ነጻነታ቞ውን ፣ ሞራላ቞ውንና ስብዕና቞ውን ዚሚፈታተኑ አጞያፊ ቃላት እንደወሚወሩባ቞ው በመግለጫ቞ው ጠቅሰዋል።
«ይህ ድርጊት በስሜታዊነት ዹተሰነዘሹ ነው ብዬ ለማለፍ ብሞክርም ሁኔታው ኹመቆም ይልቅ ፍጹም በተደራጀ መልኩ ተኚስቷል » በማለት በመግለጫ቞ው ዚጠቀሱት አሰልጣኝ ሠውነት ፀ ሚያዚያ 5 ቀን 2005 ዓ.ም ዚኢትዮጵያ ቡና እና ዚቅዱስ ጊዮርጊስ እግር ኳስ ክለቊቜ ባደሚጉት ጚዋታ ላይ ድርጊቱ ኚቀድሞው በበለጠ መልኩ መኚሰቱን አስታውቀዋል።
ይህ ሁኔታ በማንኛውም ጊዜ በእርሳ቞ውና በቀተሰባ቞ው ላይ አደጋ ይደርሳል ዹሚል ስጋት እንዲያድርባ቞ው እንዳደሚገ በመግለጫ቞ው ገልጞዋል። በመሆኑም ስራ቞ውን ተሹጋግተው እንዲሰሩ መንግሥት ሁኔታውን ተኚታትሎ ዚማያዳግም መፍትሔ እንዲሰጣ቞ውና ፣ ለእርሳ቞ውና ለቀተሰባ቞ው ጥበቃ እንዲደሚግላ቞ው በመግለጫ቞ው ጠይቀዋል።
ዚኢትዮጵያ ቡና እግር ኳስ ክለብ ስራ አስኪያጅ አቶ ገዛኾኝ ወልዮ ጉዳዩን አስመልክተው በሰጡት ምላሜ ክለባ቞ው ዛሬ ለመገናኛ ብዙኃን መግለጫ እንደሚሰጥ በመንግስት ቁጥጥር ስር ያሉ ሚዲያዎቜ መዘገባ቞ውን ዚዘሐበሻ ወኪሎቜ አስታወቀዋል።

↧

“እያንዳንዱ ዜጋ ኚራሱ ጋር ይነጋገር” –አርቲስት ታማኝ በዹነ (በሎሳንጀለስ)

0
0

በታምሩ ገዳ (ጋዜጠኛ)

በኢትዮጵያ ውስጥ እዚተካሄደ ያለው አስኚፊ ዚሰብአዊ መብት ሚገጣ ይቆም ዘንድ እያንዳንዱ ዜጋ ዚበኩሉን አሰተዋጜኊ ሊያበሚክት እንደሚገባው እና ኚራሱ ጋር መነጋገር እንዳለበት ተገለጞ፡፡ይሄ ዹተገለጾው እርቲስት እና እክቲቬስት ታማኝ በዹነ ዚኢትዮጵያ ሳተላይት ቎ሌቭዥን ኢሳት ዚተመሰሚተበት 3ኛ አመት እና ጣቢያውን ለማጠናኹር ባለፈው ቅዳሜ ሚያዚያ 13 2013 እኀአ በ አሜሪካው ዚካሊፎርኒያ ግዛት በሎሳንጀለስ ኹተማ በተደሹገው ዚገቢ ማሰባሰቢያ ፕሮግራም ላይ በመገኘት ለተሰበሳቢዎቜ እና ለኢሳት አጋሮቜ በሰጠው አሰተያዚቱ ነው፡፡

በተለይ አርቲስት ታማኝ ዚህብር ራዲዮ ዘጋቢ ኹሆነው ኹዚህ ጾሃፊ (ኚታምሩ ገዳ )ጋር ኚገቢ ዚማሰባሰብ ፕሮግራሙ በሁዋላ ባደሚገው ቃለምልልስ “ሌላው ቢቀር ልጆቻቜን አገራ቞ውን ጥለው እንዳይሰደዱ እና በአገራ቞ው ተደላድለው እንዲኖሩ ለማድሚግ በአገር ቀት በመካሄድ ላይ ያለውን ዹግፍ ቀንበር ልንሰብሚው ይገባናል፡በሶስት ሺህ ዘመን አለም በተለያዩ ዚኢኮኖሚ እድገት ላይ ሲገኝ እኛ ግን ኹሁሉ አገር በታቜ በደመ ነፍስ በሚነዳ እና ህግ በሌለበት ብ቞ኛ አገር ውስጥ እንገኛለን፡፡” ያለው አርቲስት ታማኝ ሁሉም ዜጋ ዚበኩሉን ጥሚት ማድሚግ እንዳለበት አስሚግጊ ዹተናገሹ ሲሆን አስተያዚቱን ሲያራዝምም “እኛ እናልፋልን ነገር ግን ቢያንስ ልጆቻቜን ተድላድለው እንዲኖሩ ይህን በደል ዚማስቆም ዚሞራል ግዎታ አለብን፡ እነ ታማኝ ወይም እነ እገሌ ምን አደሹጉ? ዚሚባልበት ወቅት ሳይሆን ለምንድን ነው አገሬ ውስጥ ዘወትር ቜግር ብቻ ዹምሰማው? እንደሌሎቜ አገሮቜ መሆን ዚተሳነን ለምንድን ነው? ሲል እያንዳንዱ ዜጋ እራሱን እንደዜጋ ሊጠይቅ ግዎታ አለበት፡፡”ብሏል፡፡

አርቲስት  እና አክቲቬስት ታማኝ በዹነ

አርቲስት እና አክቲቬስት ታማኝ በዹነ


ኢሳትን ዚመሳሰሉ ነጻ ዹመሹጃ ምንጮቜ ይስፋፉ ዘንድ ምን መደሹግ እንዳለበት ዚሚያስተላልፈው መልእክት ካለ ተብሎ ኚህብር ራዲዮ ለቀሚበለት ጥያቄ አርቲስት እና አክቲቬስት ታማኝ ሲመልስ” ይህ አይነቱ ሃሳብ ነው ሊበሚታታ ዚሚገባው ኚዛሬ ሶስት አመት በፊት ኢሳት አልነበሹም:: ዛሬ ግን ጋምቀላ ውስጥ ቜግር ሲፈጠር በኢሳት አማካኝነት ትሰማዋለህ :፡ዚአማራ ክልል ተወላጆቜ ኚተለያዩ እካባቢዎቜ በግፍ ሲባሚሩ ኢሳት ላይ ወዲያውኑ ትሰማዋለህ:: በሙስሊም ወገኖቻቜን ላይ በደል ሲደርስ እንደዚሁ ኢሳት ላይ መሹጃውን ትሰማዋለህ፡፡በመሚጃ ዹተደገፈ ዜና ለማግኘት ህዝቡ አስተዋጜኊ ማድሚግ አለበት፡፡ዚህቺ እንግዲህ በሶስት አመት ውስጥ ዹተገኘ ዚሁላቜን ዚጥሚት ውጀት ነው ፡፡ ሶስት አመት በጣም ትንሜ ጊዜ ነው ፡፡ኢሳት ዚሶስት አመት ልጅ ነው ፡፡ ልጅን ስናሳድግ ደግሞ ይታመምብናል: ምግብ አይስማማውም፡ብርጭቆ ይሰብራል ይሄን ሁሉ እዚተኚታተልክ አይደል ልጅህን ዚምታሳድገው?ኢሳትም እንዲሁ ደካማ ሊሆን ይቜላል ነገር ግን ሁሉም ሰው በመተባበር ዹተሟላ ዚሚዲያ ተቋም ሊያደርገው ይቜላል፡፡ለዚህ መሰሉ በጎ ተግባራት አስተዋጜኊ ማድሚግ ዚእያንዳንዱ ዜጋ ግዎታ ነው፡፡” ብላል፡፡ በስተመጚሚሻም ዹተጠናኹሹ ስራ ለማካሄድ ምን መደሹግ አለበት? ለሚለው ጥያቄ ሲመልስ “ አያንዳንዱ ዜጋ ኚራሱ ጋር ይነጋገር:: ወደዚህ ምድር ላይ ዚምጣሁበት ተልኮዮ ምንድን ነው ? ምን አድርጌ ነው ዹምሄደው? በእዚ ወሩ ለቀተሰቀ 300 ወይም 400 ዚአሜሪካ ዶላር መላክ? በ ተሻለ ቀትውስጥ ለመኖር ወይም ዘመናዊ መኪና ለማሜኚርኚር ዚተሻለ ልብስ ለመልበስ ነው ወደዚህ አለም ዚመጣነው? እንደእኔ እምነት አገራቜን ወደ ተሻለ ደሹጃ እንድትሞጋገር ጥሚት ማድሚግ እያንዳንዱ ዜጋ በሚቜለው እና አቅሙ በፈቀደው መጠን ብሄራዊ ግዎታውን ሊወጣ ይገባል ፡፡ቁጭ ብሎ መተቜት ለውጥ አያመጣም፡፡አስተዋጜኊ ማድሚግ አለብን፡፡በምናምንበት መንገድ በምንም ይሁን ዚእኔ ፍላጎት እና ስሜት ዚሚያደላው በዚህ ላይ ስለሆነ እስተዋጜኊ ማድሚግ እፈልጋለሁ ብሎ በጉልበት ይሁን በእውቀት በምክር ሊሆን ይቜላል ፡፡ይሄ ዚጥቂት ወገኖቜ እህላፊነት ተደርጎ መወስድ ዚለበትም ፡፡ ዹሁሉም ወገን እርብርቊሜ ሊሆን ይገባል ፡፡” ብሏል::

በዚህ ዚገቢ ማሰባሰብ ፕሮግራም ላይ ለተገኙ በመቶዎቜ ለሚቆጠሩ ዚሎሳንጀለስ ኹተማ ነዋሪዎቜ ዚገዢው ዚኢሃአዲግ መንግስት ዚፕሮፓጋንዳ መሳሪያዎቜ ዚሆኑት ዹመገናኛ ብዙሃናትን ጚምሮ ኚተለያዩ ዹአገር አቀፍ እና ዹአለማቀፍ ዹዜና አውታሮቜ ያሰባሰባ቞ው በምስል እና በጜሁፍ ዹተደገፉ ማስሚጃዎቜን ለታዳሚዎቹ በማቅሚብ በኢትዮጵያ ወገኖቜ ላይ በ ሀገር ውስጥ ሆነ በውጪ ሀገራት ዚደሚሱት እና በመድሚስ ላይ ያሉትን ዘግናኝ ዹሆኑ ዚሰብአዊ መብት ጥሰቶቜን ለግንዛቀ ማስጚበጫነት ይሚዳ ዘንድ ያቀሚበ ሲሆን ሁሉም ኢትዮጵያዊ ዜጋ ለአንድ አፍታ ቆም ብሎ ዚት ላይ እንደሆንን እና በወገኖቻቜን ላይ ምን አይነት ግፍ እዚትፈጞመ እንደሆነ ሊያስተውል ይገባል ሲል ወገናዊ ጥሪውን አቅርቧል፡፡

ወጣት ሄኖክ ዚሌጥላ ግጥሙን ለታዳሚዎቜ  ሲያሰማ (ኚግራ ወደ ቀኝ ሃጄ ነጂብ መሃመድ እና አርቲስት ታማኝ በዹነ)

ወጣት ሄኖክ ዚሌጥላ ግጥሙን ለታዳሚዎቜ ሲያሰማ (ኚግራ ወደ ቀኝ ሃጄ ነጂብ መሃመድ እና አርቲስት ታማኝ በዹነ)


በገቢ ማሰባሰብ ፕሮግራሙ ላይ ዚኢትዮጵያ ሙስሊሞቜን በመወኹል ንግግር ያደሚጉት እውቁ ዚሰብአዊ መብት ተሟጋቜ ሃጂ ነጂብ መሃመድ “ ህገመንግስታዊ መብታቜን ይኹበር ያሉ ሙስሊም ወገኖቻቜን ካለፈው አንድ አመት ትኩል ጀምሮ በአገዛዙ ዚጞጥታ ሃይሎቜ ለእስራት ፡ ለግርፋት እና ለስደት ዚተዳሚጉበት ዚመብት ጥያቄያ቞ው ስር ሰዶ እና ዚክርስትና እምነት ተኚታይ ወገኖቻቜን ድጋፍ አግኝቶ አሁን ካለንበት ደሹጃ ደርሷል፡፡ኚዚህ በሁዋላ ወደ ሁዋላ መመለስ ትልቅ ስህተት ስለሚሆን በተያያዝነው ሰላማዊ ዚመብት ጥያቄ ክርስቲያኑ እና ሙስሊሙ ማህበሚሰብ እጅ ለእጅ ተያያዞ አገዛዙን በቃህ ሊለው ዚግድ ይላል፡፡” ብለዋል፡፡ ሃጂ ነጂብ ንግግራቜውን በማራዘም “ነብዩ መሃመድ ተኚታዮቻ቞ው በ1034 አመት በፊት በመካኚለኛው ምስራቅ ግድያ እና እንግልት በበዛባ቞ው ወቅት ሎት ልጃቾውን ጚምሮ ወደ ኢትዮጵያ (ሃበሻ መሬት) ሄዱ በዚያ ማንንም ሰው ዚማይበድል ክርስቲያን መሪ አለ በማለት ጎሚቀት አገሮቜ ዚሆኑትን አነ ሶሪያ እና ዹመንን ትተው ወደ ኢትዮጵያ እንዲሰደዱ አዘዋል ፡፡ ታዲያ ዹተገፉ ወገኖቜን በመቀበል ለአለም አርያ ዚነበሚቜ አገር ኢትዮጵያ ዛሬ በኛ ዘመን እንዎት አላህ ዋክበር!!( እግዜአብሄር ታላቅ ነው!!) ያሉ ዜጎቜ መብታ቞ው ተንፍጎ ይታሰሩባታል?” ሲሉ ዚወቅቱን ዚኢትዮጵያ ዚሰብአዊ መብት ሁኔታን ኚቀድሞው እንግዶቜን እንድ ራስ አድርጎ ዹመቀበል ጥሩ ባህል ጋር በማነጻጞር በጥያቄ መልክ ለመግለጜ ዚሞኚሩ ሲሆን በቀርቡ ዚገዢው ፓርቲ ለፕሮፓጋንዳ መሳሪያነት ዚሚጠቀምበት ኢቲቪ “ጀሃዳዊ ሃራካት” በሚል ርእሱ እና መልእክቱ ዚማይጣጣም ፕሮግራም በማዘጋጀት በሙስሊም ወገኖቜ ላይ ለማላገጥ ዚተጠቀመበትን ዘዮ እርቃኑን መቅርቱን አጋልጠዋል፡፡ በአሁን ወቅትም ዚእገዛዙ ዚጞጥታ ሃይሎቜ ዚታሳሪዎቜ ቀተሰቊቜን በመቅሚብ ታሳሪዎቹ ይቅርታ እንዲጠይቁ ዚማግባባት ዘመቻ መጀመራ቞ውን ገልጾው “ ለመሆኑ ዹተበደለ እና መብቱን ዹተገፈፈ ሰው በዚት አገር ነው ይቅርታ ዹሚጠይቀው ? ይህ አይነቱ አካሄድ በራሱ ዹአገዛዙ ኀፍትሃዊነትን ነው ዚሚያመላክትነው ፡፡ “ብለዋል፡፡

ሄኖክ ዚሺጥላ ዚተባለ በሎሳንጀለስ ኹተማ ዹሚኖር ወጣት “ናፍቆት” በሚል ግጥሙ በአገዛዙ ዚጞጥታ ሃይሎቜ ለእስራት ዚተዳሚገው ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ እና ህጻን ልጁ ናፍቆትን ዚውስጥ ስሜትን በሚኮሚኩር መልኩ በምናባዊ ግጥሙ አወድሷ቞ዋል፡፡ በተጚማሪም ወጣት ሄኖክ “ለምንድን ነው ዛሬ ዹምናደደው?” በሚለው በሁለተኛው ግጥሙ ዹአገዛዙ ቁንጮ ዚነበሩት መለስ ዜናዊን ኮንኗል፡፡

ዚጚሚታ ስነስርአቱ ኚመካሄዱ በፊት ዚሚያሳይ ፎቶ

ዚጚሚታ ስነስርአቱ ኚመካሄዱ በፊት ዚሚያሳይ ፎቶ


ለኢሳት ማጠናኚሪያ ይሆን ዘንድ መነሻ ዋጋው 500 ዶላር ሆኖ ለጚሚታ ዹቀሹበ አንድ ታብሌት ዘመናዊ ላፕቶፕ ኚሰባት ሺህ ዚአሜሪካ ዶላር በላይ ዹተሾጠ ሲሆን አሾናፊው ግለሰብም በሳንዎያጎ ኹተማ ለሜድሚገው ተመሳሳይ ዚገንዘብ ማሰባሰቢያ ፕሮግራም ይውል ዘንድ ታብሌት ላፕቶፑን መልሰው ሰጥተዋል ፡፡አንዲት ዚሎሳንጀለስ ኹተማ ነዋሪ በበኩላ቞ው ኢሳትን ለምደገፍ በሚደሹገው ሚብርቊሜ ላይ ዚበኩላ቞ውን አስተዋጜኊ ለማበርኚት ሲሉ በእጃ቞ው ዚፈተሉትን ዘመናዊ ሙሉ ዹአገር ልብስ ለጚሚታ እንዲቀርብላቜው ለአዘጋጆቹ ሰጥተዋል፡፡ በሎሳንጀለስ ኹተማ ዚኢሳት ድጋፍ ሰጪ አባላትም በስፍራው ዚተገኙት ሁሉንም ተሳታፊዎቜን በማመስገን ኢሳትን በሁሉም መልኩ ዹመደገፍ ርብርቊሹ እንዲቀጥል ጥሪያ቞ውን አቅርበዋል፡፡ ( tamgeda@gmail.com)
↧

ዚወቅቱ ዚኢትዮጵያ ጠላቶቜ –በገ/ክርስቶስ ዓባይ

0
0

በገ/ክርስቶስ ዓባይ  ሚያዝያ 6 ቀን 2005 ዓ/ም

አንድን  ታላቅ ሀገራዊ እንቅስቃሎ ኚአጥናፍ  እስኚ አጥናፍ ማለትም ኹሰሜን እስኚ ደቡብፀ ኚምሥራቅ እስኚ ምዕራብፀ  ወጥ በሆነ መልኩ እንዲዳሚስ ዹሚገፋፋና ዚሚያስገድድፀ አሁን እንዳለንበት ወቅት ያለ ፈታኝ ሁኔታ ሲኚሰትፀ በቅድሚያ መታወቅ ያለባ቞ውንና ጥንቃቄ ዚሚያስፈልጋ቞ውን ጉዳዮቜ ለይቶና አበጥሮ ደሹጃ በደሹጃ ማስቀመጥ ግድ ይላል ።

ስለሆነም ኚጞጞት ለመዳን ዚሚያስቜለንን ሐቀኛና ፍትሐዊ ዹሆነ መመዘኛ ጊዜ ወስደን  አስበንና አሰላስለን ማስቀመጥ ይኖርብናል። በዚህ አጋጣሚ ለሰላምፀ ለፍትሕፀ ለዲሞክራሲና ለዕኩልነት እንዲሁም ሐሳብን በነፃነት ዚመጻፍና ዚመግለጜ መብትፀ ማንኛውም ኢትዮጵያዊ ዜጋ ሰላማዊ እስኚሆነ ድሚስ በዚትኛውም ዚኢትዮጵያ ምድር ተዘዋውሮ ዚመሥራትፀ ሀብት ዚማፍራትና በመሹጠው ዚአገሪቱ ክፍል ዹመኖር መብት ሊኖሹው ይገባል በማለት ዚሚያምንፀ ፍትሐዊ አስተሳሰብ ያለው ዜጋ ሁሉፀ በሃይማኖትፀ በቋንቋፀ በጎሣፀ በክልልም ሆነ በጎጥ እንዲሁም በድርጅትም ቢሆን ሳንኚፋፈልፀ በዚህ መርህ እስማማለሁፀ ለዚህም መኹበር እታገላለሁፀ ዹሚል አገር ወዳድ ኢትዮጵያዊ ለዚህ ዚጋራ ዓላማቜን  እውን መሆንፀ ዚምንኖርበት ዚቊታ ርቀትም ቢሆን ሳይበግሚን በዚአለንበት  በአንድ ላይ ሆነን መቆም አለብን።

እንዎት ?ብሎ መጠዹቅ ይቻላል።

eprdfኹሁሉም በፊት ቅድሚያ ልንሰጠው ዚሚገባን ነገር ዚአገራቜን ጉዳይ መሆን ይኖርበታል። አገር ማለት ደግሞ ወገን ማለት ነው። እዚህ ላይ ግልጜ ማድሚግ ዚሚገባን ጉዳይ ይኖራል። በተለይ ሀገርና አገር ዚተለያዩ መሆናቾውን ልናስተውል ይገባል። ሀገር ማለት በተደሚሰበት ዚጋራ ስምምነት ወይም በኃይል ዹተሰመሹ ድንበርፀ ወይም ለግዛት እንዲያመቜ ዹተዘጋጀ (Political Boundary)ራሱን ዚቻለ መጠሪያ ያለው ዚፖለቲካ ክልል ሲሆንፀ ይህም በአብዛኛው ዚሚያተኩሚው በዱር በገደሉ ፀ በጫካውና በሞለቆውፀ እንዲሁም በተራራውና በሜዳው ላይ ነው። ኹዚህም ዚተነሣ በተለይ አምባገነኖቜ ሁሉንም ነገር ትተው አገር ዹሚለውን ሳይሆን ሀገር ዹሚለውን አጉልተው ለማሣዚትና አገር ዹሚለውን ጜንሰ ሐሳብ አሳንሰውና አኰስሰው ለማሳዚት ያላደሚጉት ጥሚት ዚለም። ለምሳሌም ብናነሳ ዚወያኔው ዋና ጠርናፊ ዚነበሩት በቅድሚያ ሁሉን ሲጠቀልሉ ቆይተው አሁን ዚተጠቀለሉት መለስ ዜናዊ ዚአዲስ አበባን ዩኒቚርስቲ ምሁራንን አስመልክቶ እነዚህ ምሁራን ያለአግባብ ኚሥራ ሲባሚሩ ማን ሊያስተምር ነው ሲባሉ “መንገዱን ጹርቅ ያድርግላ቞ው” ማለታ቞ው አይዘነጋም።  በተጚማሪም ለሱዳን ወደ 65 ኪሎሜትር እርዝመት ያለው በአገር(በወገን) ያልተመኚሚበት መሬት ኚልለውፀ ዚሱዳን መንግሥት በትግል ጊዜ ላደሹገላቾው እገዛ እንደ ካሣ መስጠታ቞ው ይታወቃል። ሌላም መጹመር ይቻላል።

 

ዚትግራይን ክልል ለማስፋት እና ዚአማራውን ክልል ለማሳነስ ሲባል ራያን ኹወሎ ፀ ጠለምትንናፀ ቆላ ወገራንናፀ ወልቃይት ጠገዮን ኹጎንደር እንደ ዳቊ በመቁሚስ ወደ ትግራይ አድርገዋልፀ ቀንሻንጉልን ግማሹን ኹወለጋ ግማሹን ኹጎጃም በውሰድ አዲስ ኹልል ፈጥሚዋል። ድቡብንም እንዲሁ ኚሞዋፀ ኚሲዳሞ ኹጋሞ ጎፋ እና ኹኹፋን ኹጂማ በመቀናነስ ፈጥሚዋል። በአጠቃላይ ይህ ዓይነቱ አኹላለል ለሕዝብ እንዲጠቅም ታስቊ ሳይሆን ቀደም ሲል ዹነበሹውን ሥር ዹሰደደ ዚማንነት ጥንካሬና በራሥ ዹመተማመን  አንድነት በመሾርሾር ፍጹም ያልነበሚና ኚቶ በኢትዮጵያዊ አእምሮ ሊታሰብ ዚማይቜል ዹመኹነና ዚያንዳንዱን ዜጋ ህልውና ዚሚፈታተን ሰይጣናዊ ዹሆነ እርምጃ ነው። በእነርሱ አባባል ለሌላው ኢትዮጵያዊ “ዚመቶ ዓመት ዚቀት ሥራ” በመስጠት በዚህ ግርግር ውስጥ ግን እነርሱ ያሻ቞ውን እንዲያደርጉና እንደፈለጉ ዹአገርን ሐብትና ንብሚት እንዲዘርፉ መንገዳ቞ውን አስተካክለው ጹርሰው ዚአስፓልት ንጣፍ ሊያነጥፉ በተዘጋጁበት ወቅት ሕዝቡ ያለፉትን ዚሃያ ሁለት ዓመታት ቆይታውን እንደገና መሹምር ሲጀምር ነውፀ በተለይ ዹነፃ ሚዲያ ዹሆነው ተወዳጁ ኢሳት አገልግሎቱን በማስፋፋት አስተማማኝ መሚጃዎቜን ማሰራጚት ኹጀመሹ በኋላ ነው ሕዝቡ ኹዕንቅልፉ እንደነቃ ሁሉ መባነን ዚጀመሚው።  በተለይ ወያኔ መራሹ ዚትግሬ ባንዳዎቜ ስብስብ  ዘራፊ ሥርዓት ብዙ ዹዋሃንን አጭበርብሮ በትሚ መንግሥቱን ሲቆናጠጥ ዚወሰዳ቞ውን በማር ዹተሾፈኑ አንዳንድ እርምጃዎቜ ማስታወሱ ተገቢ ይሆናል።

ለምሳሌም ያህል ዚኊሮሞ ሕዝብ ታላቅ እንደመሆኑ መጠን ለዚህ ሕዝብ ዹሚሆን ዚቀት ሥራ ወዲያውኑ ነበር ዚተሰጠው።  ይኾውም ለሥልጣንና ለገንዘብ ጥቅም ያጎበደዱ አንዳንድ ኚሐዲ ዚኊሮሞ ተወላጆቜን አቶ ሐሰን አሊን ጚምሮ ዹተወሰኑ ሰዎቜን በማሰልጠን ዚኊሮሞን ዹተኹበሹውን ባህልና ዚገዳ ሥርዓት ኚፊት ለፊት በማስቀደም እዚሰበኩፀ ዹግዕዝ ፊደል ለኊሮምኛ ቋንቋ አይሆንም ኚእንግዲህ በኋላ ኊሮምኛ ዚሚጻፈው በላቲን ነው በማለት ማስተማር መጀመራ቞ውን በቁጭት ዚምናስታውሰው ነው።ፀ

በወቅቱ አንድ ዹማውቀው ዚቅርብ ጓደኛዹ ኊሮሞ በመሆኑ በሚሠራበት መ/ቀት ይህንኑ “ቁቀ” ብለው ዚሰዚሙትን ዚላቲን ፊደል አጠቃቀም እንዲሠለጥን ዹደሹሰውን ትዕዛዝ ቀመስ  ግብዣ ተቀብሎ ሄዶ ነበርፀ ነገር ግን ሥልጠናውን ሳይጚርስ እሳት ለብሊ እሳት ጎርሩ እዚተናደደ  አቋርጩ በመመልሱፀ ምነው ዹኹፋህ ትመስላለህሳ ? ብለው ጓደኞቹ ሲጠይቁት ዹመለሰው መልስ ዚሚሚሳ አይደለም።

እነዚህ ሰዎቜ ዓላማቾው ምን እንደሆነ አልገባኝምፀ ዚሚሠሩትንም ዚሚያውቁ አይደሉም። ዚኊሮሞ ሕዝብ ዹሚፈልገው ዚሥርዓት ለውጥ እንጂ ዹፊደል ለውጥ አይደለም ደግሞስ ቢሆን ዚተለያዩ ድምፅን በመወኹል ዚላቲን ፊደል እንደ ዹኛው ዹግዕዝ ፊደል ዹበለጾገ አይደለም።ለምሳሌም እንደ ቀፀ ቞ፀ ኘፀ ዠፀ ጠፀ ጚፀ ጞፀ ጰ ዚመሳሰሉ ፊደላት እንኳ ዚሉትም ታዲያ በምን መስፈርት ነው ዚላቲን ፊደል አጠቃቀም ተማሩ ተብሎ ዚኊሮሞ ሕዝብ ዚተወሰነበት ?በማለት ጠይቋል።

አዹይዞም በሊስት መስመር በግዕዝ ፊደል ዚሚጻፈው ኊሮምኛ በላቲን ኹሆነ ሲ቞ኚቜኩ መዋል ነውፀ አንድ ገጜ ገደማ ይፈጃል ስለዚህ አጠቃላይ ሁኔታው ዚኊሮሞን ሕዝብ ዕድገት ሆነ ተብሎ ለመግታትፀ ወይም ደግሞ ምስጢሩ ያልታወቀ ዚቀት ሥራ ሳይሆን አይቀርም  እኔ ግን በዚህ በማይሚባ ጉዳይ ጊዜዹን አላጠፋምፀ ሌላውም  ዚኊሮሞ ሕዝብ ቢሆን በዚህ ተታሎ ጊዜውንና ገንዘቡን ማጥፋት ዚለበትምፀ በማለት በመናገሩ ዚት እንደደሚሰ አይታወቅም።

 

ለማንኛውም አገር ግን ኹዚህም በላይ ታላቅ ትርጉም ያለው ጉዳይ ነው። ቀደም ሲል እንዳዚነው ሀገር ሕዝብን አይጚምርም። አገር ስንል ግን ቅድሚያ ዚሚመጣው ሕዝቡፀ ቀጥሎም ያ ሕዝብ ዚሚኖርበት መሬት (ሀገር) እና ዚአኗኗሩ ሁኔታፀ ዚአስተዳደሩ ፀዚባህሉ ፀዚኢኮኖሚውፀ ዚሃይማኖቱፀ ዚፖለቲካውና ዚጀናውን ሁኔታ ሁሉ ያጠቅልላል።

እንግዲህ እስኚዚህ ድሚስ በተደሹገው ማብራሪያ ዚምንግባባ ኹሆነ ሁሉም ኢትዮጵያዊ ላለፉት ሃያ ሁለት ዓመታት በቀጥታም ሆን በተዘዋዋሪ ትግራይ በቀል በሆኑ ጥቂት ደቂቀ ባንዳ ስብስቊቜ ኹዘር ባገኙት አስነዋሪ ዹአገር ክህደት ውርስ ዚደሚሰባ቞ውን ዚበታቜነት ስሜት ተንተርሰው በጀግኖቜ አባቶቻቜን መስዋዕትነት ዳር ድንበሯ ተኚብሮ ለብዙ ሺህ ዓምታት ታፍራና ተክብራ ዚቆዚቜውን ኢትዮጵያን ለማፈራሚስና ለመበታተን ያልፈነቀሉት ድንጋይና ያልሞሚቡት ሀራ ዚለም።

እዚህ ላይ ዚወያኔን አንዱን ዚማስመሰያ መሠሪ ተንኰል ዹሆነውን ዚብሄር ተዋጾዖን ዚተመለኚትን እንደሆነ ዓላማው  ለሀገርና ለወገን ዹሚጠቅም ሊመስለን ይቜላል። ሐቁ ግን በብሄር ተዋጜዖ ሲባል ዚቜሎታ መለኪያ ዋጋውን ያጣል። ያም ዹሚወኹል ሰው ቢማር ባይማር ግድ ዹለም ቢቻል እንዲያውም ባይማር ይሻላል። ምክንያቱም ዚቀሚበለትን ሁሉ ያለምንም ጥያቄ ዚተጻፈውን ይፈርማል፡ ዚታዘዘውን እንዳለ ተቀብሎ ይፈጜማል ያስፈጜማል። ሌላው ቀርቶ ወንድሙን ግደል ቢባል ይገድላል። አውቀው ደግሞ በተለያዬ ዚጥቅም መሚብ ውስጥ እንዲገባ ያደርጉትና ኚዚያ በኋላ በሰው አእምሮ ሊታሰብ ዚማይቜል ነገር እንኳ ቢሆን እንዲሠራ ይገደዳል። ለምሳሌ ም/ጠ/ሚ/ርና ዚትምህርት ሚ/ር ደመቀ መኰንን ዚኢትዮጵያን ግዛት ለሱዳን ለማስሚክብ ኢትዮጵያን ወክለው ዹፈሹሙ መሆናቾው በስፋት ይወራል።  ይህ ጉዳይ እውነት ኹሆነ ግለሰቡ ቢታሠሩፀ አለበለዚያም ኹነ ክብራ቞ው ቢሞቱ ይሻላ቞ው ነበር ። ግን ወያኔ እርሳ቞ውን በጊዜያዊ መቅቡጥ አታሎ እንደሮቊት ወይም እንደ ለማዳ ውሻ ተጠቅሞባ቞ዋል።

ዹ97 ዓ/ም ምርጫን ተኚትሎ በተፈጠሹው ዚምርጫ ውጀት አይደግ (ኢሕአዎግ) በዝሚራ መሾነፉ አይዘነጋም። ይሁን እንጂ አይደግ በጠመንጃ ያገኘሁትን ሥልጣን በካርድ ልነጠቅ አልቜልም በማለት ዚሕዝቡን ድምጜ ዋጋ አሳጥቶታል ። ይህንኑ ተኚትሎ በተፈጠሹው ዹተቃውሞ ሰልፍ ላይ አሁንም አይደግ ሆዬ በዚህ አጋጣሚ ሕዝቡን ለመበቀል በድብቅ ዹነፃ እርምጃ ትዕዛዝ አስተላልፎ ኖሮ ይህንኑ ተግባራዊ እንዲያደርጉ አነጣጥሮ ተኳሟቜን አሠማርቶ እንደነበር ይነገራል።

ታዲያ ነፍሰ ገዳዮቜ ተብለው ዚተመደቡት ዚመጀመሪያውን ዙር ትዕዛዝ አኹናውነው እንደተመለሱ በተደሹገ ግምገማፀ አንዳንዶቹ ባደሚጉት ገለጻ “እኔ ይህን ያህል ጥይት ተኩሌ ይህን ያህል ሰው ገድያለሁፀ እገሌ ግን እንኳን ሰው ሊገድል  አንዲት ጥይትም አልተኰሰም” በማለት እነዚሁ ሮቊቶቜ ድርጊታ቞ውን እንደጀግንነት ሲያቀርቡ ሌሎቜ ግን “በማን ላይ ነው ጥይት ዚምተኩሰው? ጠላት ላይ ቢሆን እሺፀ ያ ሌላ ጉዳይ ነው ግን በሰላማዊ ሕዝብ ላይ ያውም በወገን ላይ እንዎት ተደርጎ”  ይላሉ። ጥይት ዚተኮሱት ወደ ሌላ ክፍል እንዲሄዱ ይደሹጋል ።ኚዚያም ጥይት ያልተኮሳቜሁ እዚሁ ቆዩ ተጚማሪ ገለጻ ይደሚግላቜኋል ይባሉና እንግዲህ ተጚማሪ ዙር ስላለ በዚያን ጊዜ ትታያላቜሁ ይህ ዚመንግሥት ተዕዛዝ እስኚሆነ ድሚስ ግዳጃቜሁን መፈጾም ይጠበቅባቜኋል ተብለው ይሰናበታሉ።

ጥይት ተኩሰናል እያሉ ለተገመገሙት ነፍሰ ገዳዮቜ ዚተሰጣ቞ው መመሪያ ደግሞ ዚተለዬ ነበር። እናንተ ለመንግሥት ያላቜሁን ታማኝነት በግልጜ አስመስክራቜኋልፀ አይደግም ለእናንተ ያለው ክብር ኹፍተኛ መሆኑን ልናሚጋግጥላቜሁ እንወዳለን።

ይሁን እንጂ እነዚህ ኚሐዲዎቜ ዚተሰጣ቞ውን ግዳጅ በብቃት አልተወጡም ስለሆነም ኚዛሬ ጀምሮ ለድርጅታቜን ብቻ ሳይሆን ለእናንተም ጠላቶቜ ስለሆኑ መወገድ አለባ቞ው።

አሁን ለሁለትኛው ዙር ስትወጡ ኹኋላቾው በመሆን ጭንቅላት ጭንቅላታ቞ውን እንድትሏ቞ውፀ ዹሚል ቀጭን ትዕዛዝ መሰጠቱና በኋላም ተፈጻሚ እንደሆነ ይነገራል። ይህም እንደገና ለአይደጎቜ እንደ መኚራኚሪያ ነጥብ ሆኖ መቅሚቡ ይታወቃል። ይኾውም ኹሰላማዊው ሕዝብ በተተኮሰ ጥይት ዚመንግሥት ወታደሮቜ ተገድለውብናል ዹሚል ነው ። እንግዲህ እንደዚህ ያለ ጅብ ዹሆነን መንግሥት በዘርና በጥቅማ ጥቅም እዚተሞነገሉ ሕሊናን በመሞጥ መደገፍ ዚሞት ሞት ነው።

 

እዚህ ላይ ርዓዬ ቢሱፀ ሟቹ ጠ/ሚር በአንድ ወቅት ዚተናገሩትን ለመጥቀስ እገደዳለሁ። እኛ ዹምንፈልገው ታማኝነት ብቻ ነው እንጂ ባይማርም  ታማኝ እስኚሆነ ድሚስ ጄኔራልም መሆን ይቜላል ማለታቜውን ሐቀኛ ኢትዮጵያውያን በቁጭት ዚምናስታውሰው ነው። እዚህ ላይ ዋናው ጉዳይ ያዘዝነውን ብቻ ሳይሆን ያስብነውን ዚሚሠራ ማለታ቞ው እንደሆነ ግልጜ ነው።  ይህንን ዹመሰለውን ግልጜ ዹሆነ ዚዘቀጠናፀ በትዕቢት ዹተወጠሹ አነጋገር ሲጠቀሙ ዚነበሩትን ሰው ዹ
 ራዕይ እናስቀጥላለን እያሉ ሲደሰኩሩ ዝም ብለን እያዳመጥና቞ው ነው። እነርሱማ መያዣው መጚበጫው ቅጥ አምባሩ ስለጠፋባ቞ው ቢሉም አይደንቅም ፀ ምክንያቱም ካፈሩና ኚደነገጡ ውለው አድሚዋል።

እኛ ግን ኚነርሱ ዚባሰ ዹህሊና ስብራት ደርሶብናል። ምክንያቱም ስለ እነርሱ  መጥፎነት ብቻ ስናወራ ይኾው ድፍን ሃያ ሁለት ዓመት ሆነን። ወገናቜንም አቅጣጫና መሥመር አስይዞ ዚሚመራው ቁርጠኛ ድርጅት እስኪመጣ ድሚስ በተጠንቀቅ እዚተጠባበቀ ይገኛል።

ስለሆነም በአሁኑ ወቅት መቅደም ያለበት ምን እንደሆነ ሁሉም ኢትዮጵያዊ ጠንቅቆ አውቆታል። ሁሉም ዚፖለቲካ ድርጅቶቜ ለአገር ዕድገትና ብልጜግና እንዲሁም ለዲሞክራሲና ስብዓዊ መብት መኹበር ዹተቋቋሙ እንደመሆና቞ው መጠን ኚሁለት ጥቃቅን ጉዳዮቜ በስተቀር ሊታሚቁ በሚቜሉ መርህ ላይ ዚተመሠሚቱ እንደሆነ ይታወቃል።

እነርሱም አንደኛው ያቋቋሙት ፓርቲ መጠሪያናፀ ለሥልጣን ያላ቞ው ዚጉጉት መጠን ና቞ው። መቌም ቢሆን በዲሞክራሲ እናምናለን ዹሚሉና ለዚህም መኹበር እንታገላለን ዹሚሉ ኹሆነ ለሥልጣን ያላ቞ው ፍላጎት በሕዝብ ዘንድ ባላ቞ው ታማኝነትና ክብር ላይ ዹተመሠሹተ እንዲሁም በሕዝበ ውሳኔ ዚሚሚጋገጥ በመሆኑ ዚሥልጣን ጉጉት እዚህ ላይ ያኚትማል። ዚድርጅታ቞ውን መጠሪያ ግን ኹፈለጉ እንደያዙ በዚያው በጀመሩት ዹዕዝ ስንሠለት መቀጠል ይቜላሉ ግን ማዚት ዚሚገባ቞ው ጉዳይ አለ።

 

በተናጥል ብዙ ቢደክሙም ለውጥ ማምጣት ያለመቻላ቞ውን ዚተገነዘቡ ስለሆነ ኚሌሎቜ ተቃዋሚ ፓርቲዎቜ ጋር ተቀናጅቶ መሥራትና ይህን ራሡ ላወጣው ሕግ እንኳ ዹማይገዛ አምባገነን ሥርዓት ኚሕዝብ ጫንቃ ላይ አውርዶ በመቅበር በምትኩም በሁሉም ኢትዮጵያዊ ዘንድ ዹሚናፈቀውን ሰብአዊ መብት ዚሚኚበርበትፀ ሕግና ፍትህ ዚሠፈነበት መንግሥት እውን እንዲሆን ሌት ተቀን መሥራትን ይጠይቃል። ኚዚያ በኋላ ቜሎታውና ፍላጎቱ እስካለ ድሚስ ሥልጣኑም በአስተማማኝነት ሊመጣ ይቜላል። ምክንያቱም ዚሕዝብ ድምፅ ተቀባይነት ስለሚኖሚው ተወዳድሚው ካሞነፉ ሥልጣንም ሊይዙና ለወገን ዹሚጠቅም ራዕያ቞ውን ተግባራዊ ኚማድሚግ ዚሚያግዳ቞ው አንዳቜም መሰናክል አይኖርም።

ነገር ግን ቁምነገርኛ መዥገር ቆርበት  ነክሶ ይሞታል እንዲሉ በዚያው ባለሁበት እቀጥላለሁ ቢሉ ሕዝብ ኹጎናቾው ኹሌለ ብቻ቞ውን እንደሚቀሩ ኹአሁኑ ማወቅ አለባ቞ው። ዹሁሉም ተቃዋሚ ፓርቲ መሪዎቜና ዓባላት መነጋገርና መወያዚት ያለባ቞ው ዚወቅቱ ሁኔታ ኚዚትኛው ፓርቲ ጋር ብንቀናጅ ተስማምተንና ተግባብተንፀ በመሚዳዳት ሥራቜንን አንድ እርምጃ ወደፊት ማስኬድ እንቜላለን በሚለው ላይ ጊዜና ትኩሚት ሰጥተው  መነጋገር ይጠበቅባ቞ዋል። አስፈላጊ ኹሆነም ኚተለያዩ ፓርቲዎቜ ዚተለያዩ ሰዎቜን በመጋበዝ ስለእነርሱ ፓርቲ ገለጻ እንዲያደርጉላ቞ው ማድሚጉ ተገቢ ነው።

ያሉትን ዹተቃዋሚ ፓርቲዎቜ በማሰባሰብ ወደ አንድ ዚሚመጡበትን ዘዮ መቀዚስ ካልሆነ በስተቀር ኚእንግዲህ ወዲህ ሌላ አዲስ ድርጅት ወይም ፓርቲ ማቋቋም ማለትፀ ዚጠላትን ዕድሜ ለማሳጠር ሳይሆን ለማስሚዘም ብሎም በኢትዮጵያ ሕዝብ ላይ መቀለድ ስለሚሆን ኚቶ መታሰብ እንኳ ዚለበትም እላለሁ።

አሁን ዚሚያስፈልገው ሁሉም ተቀራርቊ መሥራትናፀ ለዚህ ቜግሩና ኑሮው  ላንገፈገፈውና በተጠንቀቅ ለሚገኘው ወገናቜን አቅጣጫ በማስያዝ መንገዱን መምራት ብቻ ነው። ነገር ግን ዚተባና ወጥ ዹሆነ አመራር ለመስጠት ዚግድ ማዕኹል መፈጠር አለበት።

ለምሳሌም ክርስቲያኑ ሕዝብ በወያኔ ጣልቃ ገብነት ለተመሹጠው ፓትሪያርክ ያለውን፡ተቃውሞ ለመግለጜ ሁኔታዎቜ እስኚሚስተካኚሉ ድሚስ ሙዳዬ ምጜዋት ዚሚባል ነገር ለቀተክርስቲያን መስጠቱን እንዲያቆም መቀስቀስፀ ትልቅ ሚሳይል እንደመትኰስ ይቆጠራል። በአንፃሩ ግን መለመን ለአፈሩ ቜግሚኛ ሰዎቜና በቀተ ክርስትያን ዙሪያ ወድቀው ለሚለምኑ ወገኖቜ እንዲመጞውቱ  ማስተማር። ጠንኹር ያለ አቅም ያላ቞ውን ደግሞ ድርጅቶን እንዲሚዱ ማበሚታት።

 

በተለይ ወጣቱ ክፍል በአብዛኛውፀ አይደግ ሥልጣን ሲይዝ ዹ10 እና ዹ8 ዓመት ዚነበሩ ሁሉ በአሁኑ ሰዓት ዹ30 ዓመት ዕድሜና ኚዚያም በላይ በመሆናቾው እነርሱን በኹፍተኛ ደሹጃ እዚተጠቀመባ቞ው ይገኛል። ስለሆነም ይህ ወጣት ትውልድ አገሩ ያለቜበትን ወቅታዊ ሁኔታ በትክክል እንዲያውቅና ዘመኑ ያመጣ቞ውን ዹመገናኛ ዘዎዎቜ ማለትም ኢንተርኔትፀ ዩቲዩብፀ ኢሜይልፀ ፌስ ቡክፀ ትዊተርፀ ስካይፕና ቫይበር ዚመሳሰሉ ዹመገናኛ ዘዎዎቜን እንዲጠቀም በማስተማር በመርዳትና በማደፋፈር መሚጃዎቜን ዚመቀበልፀ ዚመዘገብፀ ዚማስተላለፍና ዚማሠራጚት ቜሎታ቞ውን እንዲያዳብሩ ማስተማር ይጠበቅባ቞ዋል።

ኚዚያም በተጚማሪ ኚልባ቞ው አምነውበት ሳይሆን ለዕለት ጉሮሮአ቞ው ማለትም ቀተሰባ቞ውን ቜግር ላይ ላለመጣል ብለው በሥርዓቱ ታቅፈው ያሉትን በዘዮ በመቅሚብና በማግባባት አይደግ በቀጣይ ሊተገብራ቞ው ያሉትን ምስጢራዊ ዕቅዶቜ በማወቅ ለመገናኛ ብዙኃን እንዲደርሱና በወቅቱ ለሕዝብ ይፋ ዚሚሆኑበትን መንገድ ማመቻ቞ት። ነገር ግን በዚህ ሁኔታ ዚማይተባበሩትን ዹአገር ኚሐዲ ባንዳዎቜ ኚዚትኛው ቅርንጫፍ ማለትምፀ ኚብአዎንፀ ኚኊሕዎድፀ ወይንም ኹደሕዮግ መሆናቾውን ለይቶፀ ዕድሉም ዚተሰጣ቞ውን ዕለትና ቀን  ጭምርፀበጥንቃቄ በልዩ ሠነድ መዝግቩ መያዝ።

እንደሚታወቀው ዚመጀመሪያው ዚቅርብ ጠላታቜን ኹላይ በተጠቀሱት ዹአይደግ ቅርንጫፎቜ ውስጥ ተሰግስገው ለጊዜያዊ ጥቅም ሲሉ ወገናቾውን ዚሚያሰቃዩ ዚመጀመሪያ ጠላት መሆናቾው መታወቅ አለበት። ምንም እንኳ ትዕዛዙንና መመሪያውን ዚሚያወጣው ወያኔ ቢሆንም ይህንን መመሪያ ዚሚፈጜመውና በወገኑ ላይ አሰቃቂ ሥቃይፀ ዘሹፋና ግድያ ዚሚፈጞመውፀ በኊሮሞው ላይ ኊሕዎድፀ በአማራው ላይ ብአዎንፀ በደቡብ ሕዝብ ላይ ደሕዮን እንዲሁም በቀሩት ኢትዮጵያውያን ላይ ዹአጋር ድርጅቶቜ ዓባላት ስለሆኑ ባለፈው ሥራ቞ው ተጞጜተው ስማ቞ውን ለማደስ ኹወገናቾው ጎን ካልተሰለፉ በስተቀርፀ እነዚህ አካላት ኚወያኔ በኹፋ መልኩ ኚሞራል አኳያ ዚእኛነት ስሜት ዹሌላቾው ጚካኝና አሚመኔዎቜ ስለሆኑ ምንም ዓይነት ይቅርታ ሊደሹግላቾው ኚቶ አይገባም።

ስለዚህ እነዚህ ዚወያኔ ፍርፋሪ ለቃሚ ውሟቜ በአንደኛ ደሹጃ በጠላትነት መታዚት አለባ቞ው። ምክንያቱም ወያኔ ዚወጣው ኚትግራይ እንደመሆኑ መጠን እነዚህን ጥቂት አገር ኚሐዲዎቜ በመርዳት ዚሥርዓቱ ደጋፊና አስፈጻሚ ባይሆኑ ኖሮ እንኳን ሃያ ሁለት ዓመት አንድ ዓመትም ሊቆዩ ባልቻሉም ነበር።

ጠላትማ ሁልጊዜም ጠላት ነውፀ

አስቀድሞ መግደል አሟክሿኪውን ነው።

ብለው አባቶቻቜን ኚልምዳ቞ው ያገኙትን ተሞክሮ እንደ መመሪያ እንድንጠቀምበት ትተውልን አልፈዋል። በዚህ ፈታኝና ወሳኝ ወቅት ኚተራ አገልጋይ እስኚ ኹፍተኛ ዚአሻንጉሊሊትነት ሥልጣን ደሹጃ ላይ ያለ ፍርፋሪ ለቃሚ ሁሉ በክብር ወደ ወገኑ ወደ ሠፊው ዚኢትዮጵያ ሕዝብ መመለስ አለበት።

ይህን ዚማያደርግ ግን በቅርቡ ዹነበሹው እንዳልነበሚ ሲሆን መድሚሻው ዚት ይሆን?

አዎ ቢያንስ ኚሁለት አንዱ መሆኑ አይቀርምፀ አንድም ንጹሃን አገር ወዳዶቜ ያለአግባብ በሚሰቃዩበት በቃሊቲ ወይም ወደ ጠርናፊያ቞ው መቀላቀል በፍጹም አይቀርም።

ባንዳን ጊዜ ኚዳው! ድል ለሠፊው ሕዝብ!

ኢትዮጵያ እንደ ቀድሞ አባቶቻቜን ሁሉ በሐቀኛ ልጆቿ አንድነቷ ጞንቶ ይቀጥላል!

↧

ማስተማር ወይስ ማደናገር? (ለተ/ሚካኀል አበበ ዹተሰጠ ምላሜ)

0
0

ታደለ መኩሪያ

tekeleስለ ሙስሊም ኢትዚጵያውያን መሪዎቜ  ለኢሳት ገንዘብ ማሰባስብ ዝግጅት ላይ  መገኘትና ስለታማኘ በዹነ ዹዋህ አነጋገር ተክለማካኀል አበበ  ለአቀሹበው ጹሑፍ ማስተባበያ ዹቀሹበ ነው።

 

ወደ ዘርዝር ሐሣቡ ኚመግባ቎ በፊት ስለአንድ ገጠመኝ ጀባ ልበላቜሁፀ ጊዜው ቢሚዘምም አይሚሳምፀ በ1969 ዓ ም ነበር። ሻለቃ ዮሐንስ ምስክር ብቻውን በምኒልክ ቀተ መንግሥት ዹኹተመውን ዹደርግ ፣ ዚካድሬ ጎራ ዹጩር ሜዳ ቀጠና አድርጓት መዋሉ ምንጊዜም ይወሳል። በዕለቱ እምድር ቁና ትሆናለቜፀ ሻለቃ ፣ኮሌኔል፣ ጅንራል ፣ ሊቀመበሩ ሳይቀሩ ኚታንክ ውስጥ እንደተጠለሉ ይነገራል። ዚካድሬው መንጋማ እንደ አሻሮ ተቆላ ተብሎለታል።

 

ታዳንስ አንድ ሻለቃ ዮሐንስ ምስክርን  ኮፍጣና ወታደር መሆኑን ዚሚያውቅ ዚዘብ ሃለፊ ሻለቃ ባሻ እሱ መሆን አለበት በማለት ሁኔታውን ያጣራል። እርሱ እንደሆነ ይደርሰበታል።  ‘ሻለቃ ዮሐንስ  ምስክር ነው! ተሹጋጉ!’ እያለ ኚአንዱ ማዕዘን ወደሌላው ይሯሯጣል። ምድሚ  ሻለቃ፡ ኮሌኔል ጅንራል ፡  ዹደርግ አባል፣ ዚአብዮት አራማጅ ካድሬ  ሳይቀርፀ በዚጠሚጎዛው፣ ቁም ሳጥኑ ተሞሞጓል። ሊቀመበር መንግሥቱም  በታንኩ ውስጥ ኩሌ ብለዋል። ዚዘብ አላፊው ሻለቃ ባሻፀ ሻለቃ ዮሐንስ ምስክር ብቻውን ይህን ሁሉ ቀውጀ እንደፈጠሚ ሲያውቅ እራሱ ኚሻለቃው በላይ ጀግና ለመሆነ ቃጣው። ወታደራዊ ሰላምታ እዚሰጣ቞ው ሁሉንም  ኚተሞሞጉበት እንዲወጡ አደሚገ። ‘አንዱ ሻለቃ ዮሐንስ ምስክር ነው እንደብርጌድ ዚዘመተብን ደርሞበታለሁ በማለት ተኩራራ፣ ልቡንም አሣበጠ። ኚዚያ በኋላማ ማን ይቻለው? ዹደርጉም ሊቀመበር ዚሻለቃነት ማዕሹግ ሰጡት። ኚእርሳ቞ው በመለስ ለማንም አልታዘዝም አለ። በደርግ ጜፈት ቀት ግቢ እንደልቡ ይፏልል ጀምሚ። ጾሹ አበዮተኛ እያለ መግደሉን አጧጣፈ።ለትንሹም ለተልቁም መሣሪያ መምዘዙን ጀመሚ።  ቀደም ያሉት ካፈጞሙት ግድያ በልጩ ለመገኘት ዚብዙሃንን ነፍስ አጠፋ። ለእርሱ ግን መልካም ሥራ ይመስለው ነበር። ሌሎቜም እንደሱ ሰው መሆናቾው ተሚሳው።    ኮሌኔል አጥናፉ አባተን እርሱ እራሱ እደገደላ቞ው ይናገራል። ዚበላዮቹን በሥልጣና቞ው እዚገባ  በእርሱ ብሶ በሥልጣኔ ገባቜሁብኝ  እያለ በራ ኚሚዩ ይል ጀመር። እንዲህ ነው ለሕግ ያለመገዛት እንደፈለጉ መፏለል።

ሁለተኛው በቅርብ ዹሆነ ነው።ነፍሳ቞ውን ይማሹውና ዶክተር ዮናስ አድማሱ ወንደማቾው ዮሐንስ አድማሱ ስለታዋቂው ጻሐፊ ዮፍህታይ ንጉሮ ሥራዎቜ ጀምሚውት ዹነበሹውን ኹፍፃሜው ደርሱ ለሕዝብ ይቀርባል።ሥነሥሚዓቱን ዚመሩት ግለሰብ ያሳዩት ዚሥነምግባር ግድፈት ትዝብት ላይ እንደጣላ቞ው ተቺው ጠቀስ አድርገው አልፈውታል። መነሻ቞ው ለሥራው ያላ቞ውን አድናቆትና ምስጋና ለማቅሚብ  ነበር።ርዕሳ቞ውም ያተኮሚው ‘ ሊስቱ ዮዎቜ’ ላይ ነበር። ዮናስ አድማሱ፣ ዮሐንስ አድማሱና ዮፍህታይ ንጉሀ። ዹነዚህን ታላቅ ዮዎቜ በመድሚክ ላይ ያስተዋውቅ ዚነበሩት ግለስብ  ባለታሪኮቹ በሕይወት ሰለሌሉ እራሳ቞ው ዚታሪኩ ፈጣሪ ሆነው መቅሚባ቞ው ነው ያናደዳ቞ው።ይህ ዓይነቱን መጥፎ ባህል መቌ ነው ዚምናስወግደው በማለት ነበር ስሜታ቞ውን ዚገለጹት።

 

 

ልጅ ተክለማርያም አበበ ጹሑፉን በቅርብ በሚያውቀው በሰባአዊ መብት ተኚራካሪ ታማኝ በዹነ ይጀምራል።ይሄውም ዚክርስቲያኑ ባዓል ሲኚበር ዚዕስልምና ሃይማኖት ተኚታይ ኢትዮጵያውያን አለመኚበሩን  ታማኝ በዹነ በመናገሩ እንደዚዋህነት ቆጥሮታል። አበው ሲተርቱ ‘ኚጥምጥሙ ይቅደም መማሩ’ ይላሉ።

 

በ1966 ዓ ም ነበር። ዚወቅቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ዚነበሩት ዚተኚበሩ እንደልካ቞ው መኮንን ነበሩ። በአዲስ አበባ ኹተማ ዚእስልምና ሃይማኖት ተኚታይ ኢትዮጵያውያን ሃይማኖታቜን ተገቢውን እውቅና ይሰጠው ብለው ሰላማዊ ሰልፍ ይወጣሉ። መሳ ለመሳ  ዚክርስትና ሃይማኖት በሰልፉ ላይ ነበር። በወቅቱ ዹ ቀ ኃ ሥ ዩኒቚርሲቲ ተማሪዎቜ ዋናኛዎቹ ሰልፉን አስተባባሪዎቜ ነበሩ።ጥያቄው ዚፍትህ መሆኑን ይሚዳሉ። ዚኢትዮጵውያን ተማሪዎቜ ኚሚደነቁበትና አክብሮት ኚሚ቞ርበት ተግባራ቞ው አንዱ ወግተኛ አለመሆናቾው ነው። አቶ ተክለሚካኀል  አበበ በእርሱ አስተሳሰብ ዚአቶ ታማኝን  ዚዋህነት ሲገልጜ ፣ብልህነቱ  ስለፍትህ ዚማያውቁ እሲኪያውቁ ቆሞ ያለመጠበቁ ይሆን?።

 

ሁለተኛው ደግሞ ለኢሳት ለሚደሹገው ዚገንዘብ አሰባሰብ ዝግጅቶቜ ላይ ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞቜ መድሚኩን ተቆጣጠሩት ፖለቲካውንም ይቆጣጠሩታል ዹሚል ሥጋት ነው። ልጅ ተክሌ በመላ ምት ላይ ተሞርክዞ ስለ ዘጠና ሚለዮን ሕዝብ ትንተና አይስጥምፀ ነውር ነው። እንዎት ነውር እንደሆነ ወርድ ብዬ አሣያለሁ።

 

ልጅ ተክሌ  ጠላት ወዳጅ ኚሚያኚበሚው ኹአበበ ገላው በኢትዮጵያን ስሙ ሲጠራ ዹማይውለው ታማኝ በዹነን አጅብህ  በትልልቅ ዚአሜሪካና ዚካናዳ ኚተማዎቜ በመድሚክ ላይ  ሰለታዚህ እነርሱን ነህ  ማለት አይደለም። ዹልጅ ተክሌንም ሃይማኖት ዹጠዹቀ አልነበሚም።  ተክሌ  ኚሃይማኖቱ በፊት ሰው መሆኑን ዚኢሳት ሰዎቜ እንደሚያውቁ እሚዳለሁ። እስልምና ተኚታይ ወንድሞቻቜንም ኚሃይማኖታ቞ው በፊት ሰው መሆናቾውን አይዘነጉም። ዹሰው ልጅና ፍተህ ሊነጣጠሉ ስለማይቜሉ ለፍትህ ዚሚታገል ሁሉ ሰው ለመሆኑ ዚሚታገል ነውና ዘር፣ ሃይማኖት፣ ቋንቋ ፣ሞያ ወዘተ ሰው ኹሆንን በኋላ ዚሚመጡ ና቞ው። ለልጅ ተክሌ ይህ ይጠፋዋል አልልምፀ በኮታ እንደ ዘር ፓለቲካ  ሃይማኖትን ለመመድብ  መሞኹር በአሁኑ ጊዜ ዚእስልምና ተኚታዩን ወገናቜንን ዚፍትህ ጥያቄ ዳር እስኚ ዳር  ማጥለቅለቁን ያለማውቁን  ያለማቁ ይመስላል።

 

እንደሻለቃው ባሻና እንደመድሚክ አስተዋዋቂው ኹዚህም ኚዚያም ተሯርጠው ስለነገሩ ጥቂት ካወቁ በኋላ በድንገት በአጋጠሚ ራስን አንድ ቊታ አስቀምጊ ኚሌሎቜ ጋር መላተሙ አይጠቅምም። ይህ ድርጅት እቀፉ ያንን ሃይማኖት አትቀፉ ፣ እንዲህ አድርጉ ለማለት  አንተ ማነህ? ዹሚል ጥያቄ ያጭራልና ኚወዲሁ ሰብሰብ ማለቱ አይኚፋም። ዚቁጥጥር ኮሚ቎ በኢሳት ውስጥ ይቋቋም ኹሆነ መቀበልም ያለ መቀበልም ዚቊርዱ ነው።ያስተምራል ወይስ ያደናግራል ምርጫው ዚእነርሱ ነው።

 

ኚዮፍህታይ ንጉሀ ስንኝ አንድ፣ ለመንገድፀ

ለጌሟው ወቀጣ አንደ ሰው አልመጣፀ

ለመጠጡ ጊዜ ኚዚጎሬው ወጣ።

ምስጋና ይግባ቞ው ለሊስቱ ‘ዮዎቜ’ ብዙ ኹዚህ እንማራለን።

 

ታደለ መኩሪያ

tadele@shaw.ca

 

 

 

 

 

 

↧
↧

ለአቡነ ማቲያስ መመሪያ ሊሰጡ ሄዱ ዚተባሉት ኣባይ ፀሃዹ ኹደጅ እንዲመለሱ ተደሹገ (ጥብቅ መሹጃ)

0
0

በሊስት ኀይሎቜ ዚተደራጀው ዹጹለማው ቡድን ‹‹ዚኣባይ ፀሃዬን አመራር›› ያቀናጃል
መመሪያው÷ ዚልዩ ጜ/ቀት፣ ዹውጭ ግንኙነት መምሪያ፣ ፕሮቶኮል፣ ጥበቃ ሓላፊዎቜን ምደባዎቜ ይመለኚታል ተብሏል

(ዚሐራ ተዋሕዶ ዘገባ እንደወሚደ)

‹‹ኣባይ ፀሃዬ ኚስኳር ኮርፖሬሜን በተጚማሪ ጠቅላይ ቀተ ክህነትን በበላይነት እንዲመሩ ኚመንግሥት ትእዛዝ ተላልፏል፡፡ ዚትግራይ ተወላጆቜ ዚግቢውን አመራር ሙሉ በሙሉ እንሚኚበዋለን፡፡ ኹዚህ በኋላ ቀተ ክርስቲያን በትግራዎት እንጂ በአማራ አትመራም፡፡ ለሚኒስትሮቜ ዹሚፈለገውን ጥቅም እያቀሚብን እናስፈጜመዋለን፡፡››
/ኣባይ ፀሃዬ ለፓትርያሪኩ ዚሚሰጡትን ‹‹አመራር›› ኚእነ ንቡሚ እድ ኀልያስ ኣብርሃ ጋራ ያስተባብራሉ ዚተባሉት በምሥራቅ ትግራይ ዚደብሚ ኣላማ አሲራ መቲራ ቅድስት ማርያም አንድነት ገዳም አበምኔት አባ ገብሚ መድኅን ገብሚ ጊዮርጊስ ዛሬ ጠዋት ዚተናገሩት/

ፓትርያሪኩ ‹‹አባ›› ነኝ ባዩን ኚግቢው እንዲያርቁላ቞ው መመሪያ ሰጥተዋልፀ ተፈጻሚነት ይኖሹው ይኟን?
መንግሥት፣ ዚቀተ ክርስቲያን አመራር፣ ካህኑና ምእመኑ ጉዳዩን ኹምር አጢነው አቋም እንዲወስዱ ተጠይቋል፡፡

አቡነ ማቲያስ

አቡነ ማቲያስ

ኚአምስተኛው ፓትርያሪክ ኅልፈተ ሕይወት በኋላ፣ ዹመንበሹ ፓትርያሪኩን ላዕላይ መዋቅሮቜ በመቆጣጠርና ለተቋማዊ ለውጥ ዚታቀዱትን ተግባራት በማምኚን÷ 1)ቡድናዊና ግለሰባዊ ጥቅሙን አስጠብቆ ለመቆዚት፣ 2)ኊርቶዶክሳዊ ማንነትን በፕሮ቎ስታንታዊ ተሐድሶ ኑፋቄ ደብዛውን ለማጥፋት በልዩ ኹኔታ እዚተንቀሳቀሰ ዹሚገኘው ዹጹለማው ቡድን÷ ኹፍተኛ ዚመንግሥት ባለሥልጣናትን በጎጠኝነት፣ በፖሊቲካዊ ታማኝነትና በጥቅም ስቊ እና አቅርቩ ማሰለፍ መጀመሩ ተዘገበ፡፡

በጠቅላይ ቀተ ክህነቱ መምሪያዎቜና ድርጅቶቜ ውስጥ በሓላፊነት ደሹጃ ዚተቀመጡ ጥቅመኞቜን ጚምሮ ዚታወቀ ሹመት ዹሌላቾውን ነገር ግን ዹሁሉ ፈጣሪና ገባሪ ለመኟን ‹‹ሥልጣን›› ያገኙ ግለሰቊቜን ዚሚያካትተው ዹጹለማ ቡድኑ÷ በፓትርያሪኩ እና በጠቅላይ ቀተ ክህነቱ ላይ ማሰለፍ ዹጀመሹው ‹‹ዚህወሓት ኹፍተኛ ባለሥልጣናትን ነው›› ተብሏል፡፡ ቡድኑ በዚህ ስትራተጂው ዚህወሓት/ኢሕአዎግን ባለሥልጣናት ተጜዕኖ በመጠቀም በማንኛውም ቊታ በተለይም በቀተ ክርስቲያናቜን ኹፍተኛ አመራር ላይ ተጜዕኖውን ለማጠናኹርና ያሻውን ለመፈጾም ማቀዱ ነው ዚተነገሚው፡፡

ይኾው ስትራተጂ ባለፉት ኻያ ዓመታት መንበሹ ፓትርያሪኩ ለክፍፍልና ትርምስ ዚተዳሚገበት፣ ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳቱ ለጥቃትና ድብደባ ዚተጋለጡበት እንደነበር ያስታወሱት ዹጠቅላይ ቀተ ክህነቱ ምንጮቜ፣ ስልቱ በመልኩ አዲስ ባይሆንም በይዘቱ ግን ቡድኑ ዹተለዹ ቁመና ይዞ ዚተደራጀበት መኟኑን ያስሚዳሉ፡፡ እንደ ምንጮቹ ገለጻ፣ ፅልመታዊ ቡድኑ ለሊስት ኀይል ተኹፍሎ በተለያዩ ግለሰቊቜ ዚሚመራ ሲሆን ዚተመሚጡ ዚመንግሥት ባለሥልጣናትን እዚተፈራሚቀ በመወትወት/በማግባባት ተመሳሳይ ጉዳይን ኚተለያዚ አቅጣጫ እያስተነተነ ስለጉዳዩ አንድ ዐይነት ቀለም/ሥዕል ለመፍጠር ግፊት ያሳድራልፀ ለኟነ ርምጃ ዚሚያበቃ ውሳኔ እንዲተላለፍ ያደርጋል፡፡ በዚህም ቡድኑና አባላቱ ለመንግሥት ቀራቢና ተቆርቋሪ፣ ለቀተ ክርስቲያን አሳቢ መስለው ጋርዮሻዊና ግለሰባዊ ጥቅማ቞ውንና ሥልጣና቞ውን ያስጠብቃሉ፡፡

ለሊስት ኀይል ዹተኹፈለውን ‹‹ዚጚለማ ቡድን›› ዚሚመሩት ግለሰቊቜ፡-

አባ ገብሚ መድኅን ገብሚ ጊዮርጊስ – በምሥራቅ ትግራይ ዚደብሚ ኣላማ አሲራ መቲራ ቅድስት ማርያም አንድነት ገዳም አበምኔት
አባ ሠሹቀ ብርሃን ወልደ ሳሙኀል – በመ/ፓ/ጠ/ቀ/ክ ዚትምህርትና ሥልጠና መምሪያ ዋና ሓላፊ
ንቡሚ እድ ኀልያስ አብርሃ – በመዋቅር ዚማይታወቀው ዹመ/ፓ/ጠ/ቀ/ክ ዚመንፈሳዊ ዘርፍ ምክትል ሥራ አስኪያጅ
በአሁኑ ወቅት በሊስት ኀይል ዚተደራጀው ዹጹለማ ቡድን ኹውጭ ኀይል ያገኘዋል በተባለ አመራር፣ ዹመንበሹ ፓትርያሪኩን ኹፍተኛ መዋቅሮቜ ለመቆጣጠር በሚያደርገው መፍጚርጚር፣ ለዓላማዬ ዕንቅፋት ናቾው ብሎ በሚያስባ቞ው ዹጠቅላይ ቀተ ክህነቱ ሓላፊዎቜና በቀናዒ ኊርቶዶክሳውያን ላይ መጠነ ሰፊ ዚስም ማጥፋት ዘመቻ እያካሄደ ነውፀ ለዚህም ዚፓትርያሪኩ ድጋፍ እንዳለው አስመስሎ ነው መቀሳቀስ ዚያዘው፡፡ እንዲያውም ኹመሹጃው ምንጮቜ አንዳንዶቹ÷ አዲሱ ፓትርያሪክ ‹‹ሳያውቁ በቡድኑ ቁጥጥር ውስጥ ገብተው በትክክለኛ መሹጃ ላይ ተመሥርተው ለመወሰንና ዚውሳኔያ቞ውን አፈጻጞም ለመኚታተል በማይቜሉበት አጣብቂኝ ውስጥ ገብተዋል›› እስኚማለት ደርሰዋል፡፡

ምንጮቹ ለዚህ ድምዳሜያ቞ው በአብነት ዚሚጠቅሱት፣ ኚዚካቲት ወር አጋማሜ አንሥቶ በቅድስት ሥላሎ መንፈሳዊ ኮሌጅ ዹቀን መደበኛ መርሐ ግብር ደቀ መዛሙርት እና በአስተዳደሩ መካኚል ዚተነሣውን ውዝግብና አያያዙን ነው፡፡ እንደ ምንጮቹ ገለጻ፣ ውዝግቡ በአጭር ጊዜ እልባት እንዲሰጠው አይፈለግም፡፡ ለዚህም ጣታ቞ውን ዚሚቀስሩት ‹‹ኚጠቅላይ ቀተ ክህነቱ በደብዳቀ ዚተሠዚመኹትና ዹሚመለኹተኝ እኔን ብቻ ነውፀ›› በሚሉት ዚትምህርትና ሥልጠና መምሪያው ሓላፊ አባ ሠሹቀ ብርሃን ወልደ ሳሙኀል ላይ ነው፡፡

ኹደቀ መዛሙርቱም ኚሓላፊዎቹም መካኚል ምንጮቹ በስም ዚሚጠቅሷ቞ውን ግለሰቊቜ በማቅሚብ ውዝግቡን ሳብ ሚገብ እያደሚጉ ይዘዋል ዚተባሉት አባ ሠሹቀ ብርሃን፣ መንግሥት በጉዳዩ ላይ ጣልቃ ገብቶ ፓትርያሪኩን እንዲያነጋግር ኚስኳር ኮርፖሬሜኑ ኣባይ ፀሃዬ ጋራ መክሹዋል ተብሏል፡፡ አባ ሠሹቀ ብርሃን ታዲያ ይህን ዚሚያደርጉት፣ በርግጥም አካዳሚያዊ መብታ቞ውንና መልካም አስተዳደርን በመጠዹቃቾው በሚኀብ እዚተቀጡ ላሉት ደቀ መዛሙርት ኚአንጀት በማዘን አይደለም፡፡

አባ ሠሹቀ ብርሃን ቜግሩም መፍትሔውም በግልጜ ዚሚታወቀውን ዹደቀ መዛሙርቱንና ዚአስተዳደሩን ውዝግብ ኚዐውዱ ውጭ እያወሳሰቡ በስም ዚተጠቀሱትን ኹፍተኛ ዚመንግሥት ባለሥልጣን ወትውተዋል፡፡ በዚህም ጥንተ ጠላታ቞ው ማኅበሹ ቅዱሳን እንደ ተቋም እና ‹‹ዚማኅበሩን ተልእኮ ዚሚያስፈጜሙ ና቞ው›› ዹሚሏቾውን ዚኮሌጁን ሓላፊዎቜ እንደ ግለሰብ በኹፍተኛ ደሹጃ ወንጅሎ (አንዱ ዚፕሮ቎ስታንታዊ ተሐድሶ ብሎግ እንደወሞኚተው) ፖሊቲካዊም አስተዳደራዊም ርምጃ እንዲወሰድባ቞ው ዚማድሚግ ፍላጎታ቞ው ዹናሹ ኟኗል፡፡ እስኚ መጪው ዹርክበ ካህናት ቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኀ በማሰንበትም ጉዳዩ ተለጥጊና ዐቢይ አጀንዳ ኟኖ ዚፈለጉት ውሳኔ እንዲተላለፍበትም ነው ዕቅዳ቞ው፡፡
ሳይገባ቞ው በተቀመጡበት መምሪያ ሚብ ያለው ቁምነገር ለመፈጾም አቅሙም ዝግጁነቱም ዹሌላቾው አባ ሠሹቀ ብርሃን፣ ለዚህ አካይስት አድራጎታ቞ውና ዕቅዳ቞ው ተባባሪ አላጡምፀ በቀደሙት ዘገባዎቻቜን እንዳስነበብነው ዹደቀ መዛሙርቱን ጥያቄ አጥንቶ ዚመፍትሔ ሐሳብ እንዲያቀርብ ዹተቋቋመው ኮሚ቎ ሥራውን እንዳይጀምር በማሰናኹል ዚሚያግዟ቞ው ዚፅልመታዊ ቡድኑ ዹበላይ ተቆጣጣሪ ንቡሚ እድ ኀልያስ ኣብርሃ አሉላ቞ው፡፡ ንቡሚ እዱ ዚፓትርያሪኩ አማካሪ መስለውና ራሳ቞ውን በአማካሪነት ሟመው በቀጣይ ዚፓትርያሪኩን ልዩ ጜ/ቀትና ዹውጭ ግንኙነት መመሪያ ለመቆጣጠር አቶ ኣባይ ፀሃዹ ለፓትርያሪኩ ‹‹ዚሚሰጡላ቞ውን መመሪያ›› ዚሚጠባበቁ ና቞ው፡፡

ለሐራዊ ምንጮቜ በደሹሰው ጥቆማ መሠሚት፣ አቶ ኣባይ ፀሃዹ ለፓትርያሪኩ መመሪያ እንዲሰጡ ማግባባት ያደሚጉት በምሥራቅ ትግራይ ዚደብሚ ኣላማ አሲራ መቲራ ቅድስት ማርያም አንድነት ገዳም አበምኔት ነኝ ዚሚሉት አባ ገብሚ መድኅን ገብሚ ና቞ው፡፡ ‹‹አባ›› ነኝ ባዩ ገብሚ መድኅን አበምኔት ነኝ በሚል በስሙ ኚሚነግዱበትና ለሀ/ስብኚቱ ኚማይታዘዙበት ገዳም ‹‹አበምኔትነት›› በቀር በመንበሹ ፓትርያሪኩ ይህ ነው ዚሚባል ሹመት ዹሌላቾው ና቞ውፀ በገዳማት ርዳታ ስም ኹፍተኛ ፈንድ ለማጋበስ ዚቋመጡባትን ዚገዳማት አስተዳደር መምሪያ ዋና ሓላፊነት ለቀም እስኪያደርጓት ድሚስ!!
ዚአሲራ መቲራው ‹‹አባ›› ገብሚ መድኅን በሜግግሩ ወቅት ፊት በሰጧቾውና አለመጠን ባቀሚቧ቞ው ዐቃቀ መንበሹ ፓትርያሪኩ ተሾጋግሹው ኚቀድሞም ባደለቡት ዚዝርፊያ ሀብት ላይ አያሌ ዹግል ሀብት ለማካበት ኹኔታዎቜን አመቻቜተዋልፀ ራሱን በዳግም አደሚጃጀት ባጠናኚሚው ፅልመታዊ ቡድን ውስጥም በቅድመ ግንባር ዚተሰለፉ፣ ስንኳን ለመነኲሎ ለሰብአ ዓለም አጞያፊ በኟኑ ዚድፍሚት ኀጣውእ ተሰነካክለው በማሰነካኚል ዚታወቁ፣ በሄዱበት ዚማይለዩትን ሜጉጥ በሠባራ ሰንጣራው ምክንያት ባገኙት ላይ (በሀ/ስብኚታ቞ው ሊቀ ጳጳስ ላይ ሳይቀር) እዚመዘዙ ዹሚደነፉ ግልፍተኛ ና቞ው፡፡

ንቡሚእድ ኀልያስ አብርሃ

ንቡሚእድ ኀልያስ አብርሃ

ዝርዝሩ ለኋላ ይቆዹንና ‹‹አባ›› ገብሚ መድኅን ባለፉት ሊስት ቀናት በአቶ አባይ ፀሃዹ ላይ አካሂደውታል በሚባለው ውትወታ÷ በፓትርያሪኩ ልዩ ጜ/ቀት እና ዹውጭ ግንኙነት መምሪያ፣ ዚፓትርያሪኩ መጋቀ ሥርዐት (ፕሮቶኮል)፣ ዹመንበሹ ፓትርያሪኩ(ዚግቢ) ጥበቃ ሓላፊ መኟን ዚሚገባ቞ውን ሰዎቜ መልምለውና አሳምነው እንደጚሚሱ ኚራሳ቞ው አንደበት በዛሬው ዕለት ሲነገር ተደምጧል፡፡ ካለፉት ኻያ ዓመታት ልምድ ለመገንዘብ እንደሚቻለው እኒህ ዚሓላፊነት ቊታዎቜ (በቀጣይ እስካልተስተካኚሉ ድሚስ)÷ ፓትርያሪኩን በመቆጣጠር፣ ባለጉዳዮቜን በማጉላላትና ዚቀተ ዘመድ ሰንሰለት በመዘርጋት አስኚፊ ሙስናና በቀተ ክርስቲያን ስም ሕገ ወጥ ተግባራት ዚሚፈጜምባ቞ው እንደነበሩ አሌ አይባልም፡፡

ለአስሚጅነት እንዲኟን ኚሙስናውም ኹሕገ ወጥ ተግባሩም አብነት እንጥቀስ፡፡ ፓትርያሪኩ እንደተሟሙ ሰሞን ‹‹አላምዳለኹፀ አማክራለኹ›› በሚል ተጠግተው ቢሯ቞ውን በዚያው በጜርሐ መንበሹ ፓትርያሪኩ ያደሚጉት ንቡሚ እድ ኀልያስ በቀተ ክርስቲያኗ ስም በሚደሹግ ትብብር ሁለት ሰዎቜን ገንዘብ ተቀብለው ወደ አሜሪካ ለመላክ ያደሚጉት ሙኚራ ተይዞባ቞ዋል፡፡

በመለያ ስሙ ‹‹ሃይለ ሰይጣን›› ዚሚባለውና በቀድሞው ፓትርያሪክ እገዛ በዋሜንግተን ዲሲና ካሊፎርኒያ አህጉሹ ስብኚት ሕገ ወጥ ሹመቶቜ ዚተደራሚቡለት ኀይለ ጊዮርጊስ ጥላሁን ኚፓትርያሪኩ ምርጫ ወቅት ጀምሮ በአዲስ አበባ ይገኛል፡፡ ሃይለ ሰይጣን ዚፓትርያሪኩ ልዩ ጜ/ቀትና ዹውጭ ግንኙነት ዹበላይ ሓላፊ ሊቀ ጳጳስ በኟኑት አቡነ ገሪማ አማካይነት ኚአዲሱ ፓትርያሪክ ጋራ ዕውቂያውንና መቀራሚቡን ማጠናኚሩ ይነገራል፡፡ ዚሥራ አስኪያጅነት ሥልጣኑ ኊርቶዶክሳዊነት በሌለው ፕሮ቎ስታንታዊ ማንነቱ ያገኘው ሕገ ወጥ ሹመት ኟኖ ሳለ፣ በልዩ ጜ/ቀትና ዹውጭ ግንኙነት ዹበላይ ሓላፊው ሊቀ ጳጳስ አስፈጻሚነትና በእነ ንቡሚ እድ አስተናባሪነት ዚቀድሞው ዚዋሜንግተን ዲሲና አካባቢው ሀ/ስብኚት ሊቀ ጳጳስና ቀናዒ ኊርቶዶክሳውያን ሠራተኞቻ቞ው ዚደኚሙበትን ሀ/ስብኚትና መንበሹ ጵጵስና ሳይገባው ለመሚኚብ ዚሚያስቜለውን ደብዳቀ ሰሞኑን አጜፎ ወደዚያው ለመብሚር ተዘጋጅቷል፡፡

ሃይለ ሰይጣን ለመልስ ጉዞ ሲዘጋጅ ዚያዘው ሰለባ ይህ ብቻ አይደለም፡፡ በቆይታው በቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ ዚታገደውንና ደርሶ ማኅበሹ ቅዱሳንን እገዳደራለኹ ባዩን ‹‹ዚጉባኀ አርድእት›› ጉዳይ ኚግንባር ቀደም ዚፕሮ቎ስታንታዊ ተሐድሶ አራማጆቜና ሌሎቜ ግብሚ አበሮቹ ጋራ በመኟንለማንቀሳቀስ መሞኚሩ ተዘግቧል፡፡ በፌዎራል ጉዳዮቜ ሚኒስ቎ር በአዲስ መልክ እንደተዘጋጀ በተገለጾው ዚሃይማኖት ማኅበራት ምዝገባ አዲስ አሠራር አግኝቶ ነገር ግን በቀተ ክርስቲያናቜን ውስጥ ለመንቀሳቀስ ኚመሰሎቹ ጋራ ጅር ጅር ሲል ሰንብቶ ነው ዚሚሄድ፡፡
ወደ ቀደመ ነገራቜን እንመለስ፡፡ ሰሞኑን ‹‹አባ›› ገብሚ መድኅንና ፅልመታዊው ቡድን በሚያካሂዱት ውትወታ ታዲያ ዹውጭ ግንኙነት መመሪያውንና ዚልዩ ጜ/ቀት ሓላፊነቱን ጠቅልለው በመሚኚብ ይመራሉ ዚሚባሉት ‹‹ሰይጣንን በዘመን እንጂ በተንኰል እንደሚወዳደሩት›› ዹሚነገርላቾው ንቡሚ እድ ኀልያስ ኣብርሃ ና቞ው፡፡ ዚፓትርያሪኩ መጋቀ ሥርዐት (ፕሮቶኮል) እንዲኟኑ አሳምኜ መልምያ቞ዋለኹ ዹሚሏቾው ደግሞ አቶ ተወልደ በኀይሉ ዚተባሉ ግለሰብ ና቞ው፡፡ አሁን በዜግነትና ኀሚግሬሜን ጉዳይ ሠራተኛ መኟና቞ው ይነገራል፡፡ ግለሰቡ በ‹‹አባ›› ገብሚ መድኅን ምልመላና ማግባባት ዚመንግሥት ሥራ቞ውን ለቀው ዚፓትርያሪኩ ፕሮቶኮል ለመኟን እንደተስማሙ ኚራሳ቞ው ኚአባ ገብሚ መድኅን በዛሬው ዕለት ተሰምቷል፡፡ ሌላው ዚአባ ገብሚ መድኅን ምልምል ለጊዜው ስማ቞ው ተለይቶ ያልተገለጞና በወቅቱ ዚግቢው ጥበቃ ሓላፊ አቶ ብርሃኔ ኀይሉ ላይ/ምትክ ዚሚሟሙ ሰው ና቞ው፡፡
በ‹‹አባ›› ገብሚ መድኅንና በጹለማው ቡድን ዕቅድ መሠሚት፣ እኒህ ሊስት ዚሓላፊነት ቊታዎቜ ተይዘው ሲያበቁ በቀጣይ ካነጣጠሩባ቞ው ዚአስፈጻሚው አካል (ዹጠቅላይ ቀተ ክህነት) ዚሓላፊነት ቊታዎቜ አንዱ ዚበጀትና ሒሳብ መምሪያው ነው፡፡ በአሁኑ ወቅት በዚህ መምሪያ ላይ እዚሠሩ ዚሚገኙት ሓላፊዎቜ ዚማኔጅመንትና አካውንቲንግ ሥልጡኖቜ ና቞ው፡፡ ኚትውፊታዊውም ኹዘመናዊውም ትምህርት ዚሌሉበት እነአባ ገብሚ መድኅን ግን እኒህን ባለሞያዎቜ አስወግደው በምትካ቞ውመመለስ ዚሚፈልጉት ገብሚ መስቀል ድራር ዚተባሉ ዚአስተሳሰብና ተግባር መሰላቾውን ነው፡፡ ኹጠቅላይ ቀተ ክህነቱ ዚበጀትና ፋይናንስ መመሪያ ኚተነሡ በኋላ በአዲስ አበባ ሀ/ስብኚት ዚቁጥጥር ሓላፊው ገብሚ መስቀል ድራር ዚሁለት ቪላዎቜ ባለቀት ኚመኟና቞ውም በላይ ለዓመታት ያካበቱት ገንዘብ ‹‹ባንኩን አጣቊታል›› በሚል ይወራባ቞ዋል፡፡
እንግዲህ እነ ‹‹አባ›› ገብሚ መድኅን÷ ‹‹ዚትግራይ ተወላጆቜ ዚግቢውን አመራር ሙሉ በሙሉ እንሚኚበዋለን፡፡ ኹዚህ በኋላ ቀተ ክርስቲያን በትግራዎት እንጂ በአማራ አትመራም፡፡ ለሚኒስትሮቜ ዹሚፈለገውን ጥቅም እያቀሚብን እናስፈጜመዋለን›› ዚሚሉት በእኒህ ስንኩል ግለሰቊቜ በሚዘወሩ ዚቀተ ክህነቱ ኹፍተኛ መዋቅሮቜ አማካይነት ነውፀ ትግራዎት በእኒህ ዚአስተሳሰብና ዚተግባር ስንኩላን ሊወኹሉም ሊጠሩም አይቜሉምፀ አይገባ቞ውም እንጂ!

ዹዜናው ምንጮቜ፣ ‹‹አባ›› ገብሚ መድኅንና ዹጹለማው ቡድን በዛሬው ዕለት አቶ ኣባይ ፀሃዬን ኚፓትርያሪኩ ጋራ በማገናኘትና ፓትርያሪኩን በማግባባት ይህንፍላጎታ቞ውን ኚዳር ለማድሚስ ዕቅድ ነበራ቞ው፡፡ አልያዘላ቞ውም እንጂ!
በእነ ‹‹አባ›› ገብሚ መድኅን ፕሮግራም መሠሚት፣ አቶ ኣባይ ፀሃዬ ዛሬ፣ ሚያዝያ 10 ቀን 2005 ዓ.ም. ኚጠዋቱ 3፡15 ላይ ወደ መንበሹ ፓትርያሪኩ ገብተው በደጃፉ ቆመው ወዲያ ወዲህ ሲሉ ታይተዋልፀ እዚመሯ቞ው ዚገቡትም ሲወተውቷ቞ው ዚሰነበቱት ‹‹አባ›› ገብሚ መድኅን ና቞ው፡፡ አመጣጣ቞ው ግን በመንገደኛው ‹‹አባ›› ገብሚ መድኅን ቀጠሮ እንጂ እንደ መንግሥት ኹፍተኛ ባለሥልጣን ወጉን (ፕሮቶኮሉን) ዹጠበቀ አልነበሹምና ዹፈለጓቾውን ‹‹መመሪያ ተቀባይ›› አላገኟ቞ውምፀ ‹‹መመሪያ ተቀባዩም ለስብሰባ ወጥተው በቢሯ቞ው አልነበሩምፀ›› ይላሉ ምንጮቹ፡፡ በርግጥ አቶ ኣባይ ‹‹መመሪያ ሊሰጧቾው ተዘጋጅተውባ቞ዋል›› በተባሉት ቅዱስነታ቞ው ምትክ እዚያው በቆሙበት በአልፎ ሂያጅ ካገኟ቞ው ሁለት ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት ቡራኬ ተቀብለዋል፡፡ ኹዚህ በቀር ጚዎታ቞ው ኚግቢው ጥበቃ አባላት ጋራ ነበርና ኚቆይታ በኋላ በመጡበት አኳኋን ተመልሰዋል፡፡

ይህም ስለሆነ ዚስኳር ኮርፖሬሜን ዳይሬክተር ጄኔራል አቶ ኣባይ በዛሬ ዕለት ወደ መንበሹ ፓትርያሪኩ መጥተው ኹደጃፍ ስለተመለሱበት ጉዳይ በግልጜ ዚተሚጋገጠው፣ ‹‹አባ›› ገብሚ መድኅን በተመለደ ግልፍተኝነታ቞ው ድምፃ቞ውን አሰምተው ሲናገሩ ካደመጧ቞ው እማኞቜ ነው፡፡ እማኞቹ ለሐራዊ ምንጮቜ እንደመሰኚሩት፣ ኣባይ ፀሃዹ በዛሬው ዕለት ወደ መንበሹ ፓትርያሪኩ ዚመጡት ለብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያሪክ አቡነ ማትያስ መመሪያ ለመስጠት እንደነበር ‹‹አባ›› ገብሚ መድኅን በበስጭት ተናግሚዋል፡፡ በአጭሩ በብዙ እማኞቜ ዚተሚጋገጠው፣ ዚትግራዎትን አስተሳሰብና ፍላጎት ፈጜሞ ሊወክልና ሊያስጠብቅ ዚማይቜለው አሳፋሪውና አሳዛኙ ዚ‹‹አባ›› ገብሚ መድኅን ቀጥተኛና አሳዛኝ አነጋገር ዹሚኹተለው ይዘት ነበሚው፡፡

‹‹ለፓትርያሪኩ አመራር ሊሰጡ ነበር ዚመጡት፡፡ ቀተ ክርስቲያን ኹዚህ በኋላ በትግራዮቜ እንጂ በአማራ አትመራም፡፡ ዚፓትርያሪኩን ፕሮቶኮል በቅርቡ አስመጥቌ ጚርሻለኹ፡፡ ዚጥበቃ ሓላፊውንም አስመጥቌ ጚርሻለኹ፡፡ ኹዚህ በኋላ በኣባይ ፀሃዬ መሪነት ቀተ ክርስቲያን ትመራለቜ፡፡ መንግሥት ኣባይን ኚስኳር ኮርፖሬሜን በተጚማሪ ጠቅላይ ቀተ ክህነቱን በበላይነት እንዲመሩ ትእዛዝ ተላልፏል፡፡ ዚትግራይ ተወላጆቜ ዚግቢውን አመራር ሙሉ በሙሉ እንሚኚበዋለን፡፡››

አቶ አባይ ጞሐዬ

አቶ አባይ ጞሐዬ

በዕሥራ ምእቱ መባቻ ሙስናን፣ ዚዘመድ አዝማድና ዐምባገነናዊ አስተዳደርን ኹጠቅላይ ቀተ ክህነቱ ለማስወገድ ተደርጎ ዹነበሹው ትግል ብፁዓን አባቶቜን በመኚፋፈል፣ ኚዚያም አልፎ በማንገላታት መምኹኑን ያስታወሱ ዹዜናው ምንጮቜ ‹‹አሁን ደግሞ አቶ ኣባይ ምን ቀራ቞ው?›› በማለት ይጠይቃሉ፡፡ ጉዳዩን መንግሥት፣ ዚቀተ ክርስቲያናቜን ኹፍተኛ አመራር፣ ካህናትና ምእመናን ሁሉ ዹምር ሊያዝኑበት እንደሚገባም ያሳስባሉ፡፡

በርግጥ በሐራዊ ግምገማ፣ ፓትርያሪኩ በጹለማው ቡድን አጣብቂኝ ውስጥ እንደገቡ መደምደሙ ኹጊዜው ዹቀደመ ይመስላል፡፡ ለምን? ፓትርያሪኩ ዹቅ/ሲኖዶሱን አቋምና ዚቀተ ክህነቱን አሠራር በጣልቃ ገብነት ዚሚያበላሹትን ‹‹ድሮም አሁንም እቃወማለኹ›› ሲሉ አሚጋግጠዋልና፡፡
‹‹ሰውን መጥላትም መውደድም ዚምንቜለው በዘሩ ሳይሆን በግብሩ ነውፀ አንድ ሰው ሊመሰገንም፣ ሊሟምም ሊሻርም ሊወቀስም ዚሚገባው በጠባዩ፣ በግብሚ ገብነቱ፣ በትምህርቱ ብቻ እዚተመዘነ መኟን አለበትፀ›› በማለት ጎጠኝነትን በዐደባባይ አውግዘዋልና፡፡

‹‹ዚተሟላና ዹተቃና ሥራ ለመሥራት ኹሁሉ አስቀድሞ ብቃትና ጥራት ያለው ሥራ መሥራት ያስፈልጋል፡፡ ለዚህ ደግሞ ሰው በሰው ላይ መደራሚብ ሳይሆን ትምህርትና ቜሎታ ያለው፣ ለተመደበበት ሥራ ዚሚመጥን ሰው መቀመጥ አለበት፡፡ ለዚህቜ ታላቅ መንፈሳዊ ተቋም ዚሚመጥኑ ሰዎቜ መቀመጥ አለባ቞ው፡፡ ቅ/ሲኖዶስ ለዚህ ጉዳይ ትልቅ ትኩሚት ይሰጠዋል ዹሚል እምነት አለኝፀ›› በማለት ትክክለኛውን ሰው በትክክለኛው ቊታ በማስቀመጥ ተቋማዊ ለውጡን ወደፊት ለማራመድ መዘጋጀታ቞ውን አስታውቀዋልና!!

↧

! 

 በለው ‘አውጫጭ’ ተጀመሹ 

.!

0
0

 
Abrham Destaባለፈው ዚትግራይ ህዝብ በምርጫ ወሚቀቶቜ ዚተለያዩ ኣስተያዚቶቜ (ኣብዛኞቹ ስድቊቜ) በመፃፍ ህወሓትን ማስጠንቀቁ ፅፌ ነበር። ያኔ ባስቀመጥኳ቞ው ቁጥሮቜ ታድያ ‘ማኖ ዚነካሁ’ መሰለኝ።

ዚህወሓት መሪዎቜ በሰጠሁት ስታትስቲክስና ዹቀበለ መሹጃ ተንተርሰው በማጣራት መሹጃ ዚወጣባ቞ው ዚምርጫ ጣብያዎቜ እዚለዩ ይገኛሉ። ይህን ያህል መሹጃ ዚወጣበት መንገድና መሹጃው ዚሰጡ ሰዎቜ ለማወቅ ‘ኣውጫጭ’ ጀምሚዋል። በተጠቀሱት አኚባቢዎቜ ዚነበሩ ዚምርጫ ታዛቢዎቜና አስተባባሪዎቜ (ሁሉም ዚህወሓት አባላት ናቾው) ‘hard ዉስጥ’ ና቞ው። (ወይኔ ድሮ ለኣውጫጭ ቅኔ ነበር መድሃኒቱ።)


በተያያዘም ህወሓቶቜ እኔ ለምፅፋቾው መሚጃዎቜ ምንጮቹ እነማን እንደሆኑ (ዚራሳ቞ው አባላት ወይ ዚዉስጥ ሰዎቜ እንደሚሆኑ ጥርጥር ዹላቾውም) ለማወቅ ‘ኣብርሃ ደስታ ዚሚባል ልጅ ኹነማን ጋር እንደሚንቀሳቀስ ኚድሮ በበለጥ ክትትል’ እንዲደሚግበት ተወስነዋል። በዚህ መሰሚት ድሮ እንዲኚታተሉኝ ኚተመደቡት ‘ዚደህንነት ሰዎቜ’ ኣሁን በሁለት እጥፍ ይጚምራሉ። እኔም ደስ አለኝፀ አጃቢዎቌ (ዞምቢዎቹ) በዝተውልኛላ።

ይሄ ስልክ መጥለፍ ምናምን ተዉት እንዎ? ወይስ ብዙ 

 መጠቀም እንደሚቻል ተገንዝበዋል? ለማንኛውም ሁለቱ ዚህወሓት/ ኢህኣዎግ ኹፍተኛ ‘ዚደህንነት ሓላፊዎቜ’ ኹፍተኛ ጠብ ላይ ና቞ው። በሁለቱ መካኚል ዹኹሹሹ ጠብ ኣለ (ስም መጥቀስ ኣያስፈልግም)። እርስበርሳ቞ው ዚሚጣሉት ያህል እኔን ኣይጠሉኝም።

ዚደህንነት ሰዎቜ ሰለማዊ ግለ ሰዎቜን ኚመኚታተል ይልቅ ሀገራዊ ፋይዳ ባላ቞ው ነገሮቜ ቢያተኩሩ ጥሩ ነው። ዚገዢው ፓርቲ ህልውና ለማስቀጠል ዚዜጎቜ መብት ኚመጣስ ይልቅ ዚህዝብን ሁለንተናዊ ደህንነት ለማስጠበቅ ቢጥሩ መልካም ነው።

 

↧

ክፉን ሰውና ክፋተኝነትን እንዎት እናውቃለን?

0
0

በ ይሄይስ አእምሮ

Penርዕሮ በጣም እንዳይጮኜብኝ ፈርቌ እንጂ ላደርገው አስቀና ፈልጌም ዹነበሹው “ሰይጣንና ሰይጣናዊነት እንዎት ይታወቃሉ?” ዹሚል ነበር፡፡ ይህ ጜሑፌ በዚሁ ተመሳሳይ ጉዳይ ዙሪያ ባለፈው ሰሞን በአንዳንድ ድሚ ገፆቜ ዚወጣውን በሎ቎ኒስቶቜ ዚሰላምታ መለዋወጫ ምልክቶቜ ምስል ዹተደገፈ አነስተኛ መጣጥፍ ዹተኹተለ  ነው፡፡ ኹሁሉ በፊት ግን ቀጣዩን ሥነ ቃላዊ ትውፊት ለነገሬ መነሻነት ባስቀድም ደስ ይለኛል፡፡

ዹቾገሹው ሰው ኚገባበት ዚቜግር ማጥ ለመውጣት ዚማያደርገው ነገር ዚለም፡፡ አንዲት ሎት፣ ልጅ መውለድ እምቢ ይላትና ለዐርባ አራቱም ታቊት ትሳላለቜፀ በዚያም አልሆነላትም፡፡ በዚጠንቋዩና በዚደብተራው ቀትም ደጅ ትጠናለቜፀ በዚያም አልሆነም፡፡ በዹጠበሉና በዚሀኪም ቀቱም ትንኚራተታለቜፀ አሁንም በዚያም አይሆን ይላታል፡፡ ቢጚንቃት ለሰይጣን ትሳላለቜ፡፡ ስለቷም “አንተ እንደኔው ዚእግዜር ፍጡር ዹሆንክ ሰይጣን ሆይ! ልጅ እወልድ ብዬ ብዙ ተሳልሁፀ ወጣሁ ወሚድሁ ግን አልሆነልኝም፡፡ አሁን ደግሞ ባንተ በኩል ልሞክር ወስኛለሁ፡፡ ስለዚህ እስኚዛሬ ዓመት ድሚስ ወንድ ልጅ ኹነቃጭሉ ኹሰጠኾኝ ራሎው ፈትዬ አንድ ቡልኮ በስለት አስገባልሃለሁ” ዹሚል ነው፡፡

ዚአጋጣሚ ነገር ሆነና ልክ ባመቱ ዹሰማ ሰምቷት አንድ ወንድ ልጅ ኹነቅጭልጭሉ ትወልዳለቜ፡፡ ደስታዋም ኚጣሪያ በላይ ይሆናል፡፡ ኚአራስ ቀት ጀምራ ትፈትልና በክርስትናው ማግሥት ለሰይጣን ዚተሳለቜውን ቡልኮ በዕውቅ ሾማኔ አሠርታ ዝግጁ ታደርጋለቜ፡፡ ነገር ግን ያላሰበቜው ቜግር ይገጥማታል፡፡ ሰይጣንን ዚት አግኝታ ትስጠው? ቜግር እኮ ነውፀ አንዱ ሲሟላ አንዱ አይሟላም፡፡

በዚመንደሩና በዚአጥቢያ አብያተ ክርስቲያን እዚዞሚቜ “ዚሰይጣንን ቀተ ‹ክርስቲያን› ያያቜሁ ነይ ወዲህ በሉኝ” ብትል ማን ዐውቆት ያሳያት? ብዙ ትለፋለቜፀ ትደክማለቜምፀ ነገር ግን በክንዷ አንጠልጥላ ዚምትዞሚውን ቡልኮ ወይም ጋቢ ዚሚሚኚባት አንድም ሰይጣን ይጠፋል፡፡

ቜግሯን ያስሚዳቻ቞ውና ዚገባ቞ው አንድ ብልህ ሜማግሌ ግን እንዲህ ሲሉ ይመክሯታል፡፡ “አንቺ ሎትዮ፣ ልጅ ለመውለድ ያደሚግሜው ጥሚት በውነቱ ዹሚገርምና ታይቶም ሆነ ተሰምቶ ዚማያውቅ ነው፡፡ አሁን ሰይጣንን ካላገኘሜውና ቀቱንም ካጣሜው በአማራጭነት እንዲህ አድርጊ፡- እሁድ ቀን ወደ አንዱ ቀተ ክርስቲያን ሂጂ፡፡ ኚዚያም ማርገጃው አካባቢ ሜማግሌዎቜ ተሰብስበው ዚተጣሉ ወይም ዚተቀያዚሙ ሰዎቜን በሚያስታርቁ ጊዜ ዚሜማግሌ ቃል አልሰማም ብሎ ንቋቾው ኚጉባኀው እመር ብሎ ዚሚወጣ ሰው ስታገኚ ‹በስምህ ዚተሳልሁትን ልሰጥህ ስፈልግህ ኖሬ ዛሬ ገና አገኘሁህፀ ይሄውልህ ቡልኮህ› በይና ትኚሻው ላይ ጣይለትፀ ሰይጣን ማለት ዕርቅና ሰላምን ዚማይወድና ዹማይፈልግ ነውና እዚያ ማርገጃው ላይ በሰው ተመስሎ ታገኝዋለሜ፡፡” ይላታል፡፡

‹ሞኝ ዚነገሩትንፀ ብልህ ዚመኚሩትን› ነውና ያቺ ሎት እንደተባለቜው ቀተ ክርስቲያን እዚሄደቜ ያን መሳይ ሰው ታጠምድ ያዘቜ፡፡ አንድ ቀንም እንደድንገት ሃሳቧ ዚሚሣካበት ምቹ አጋጣሚ ይፈጠራል፡፡ አንድ ደመ ሞቃት ሰው ዚሜማግሌዎቜን ምክርና ተግሣጜ እንዲሁም ዚማስታሚቂያ ሃሳብ ንቆ “ደግሞ እናንተን ብሎ አስታራቂ! ቀልማዳ ሁላፀ እኔ ነኝ ደግሞ ‹በድዚሃለሁና ይቅር በለኝ ብዬ እሱ እግር ላይ ዚምወድቅ?› ዚወሬ ቋቶቜ! 
” በማለት ተስፈንጥሮ ኚጉባኀው ሲወጣ ታዚዋለቜ፡፡ ይሄኔ በደስታ እዚተፍነኚነኚቜ አፈንጋጭ ጎልማሣውን ጠጋ ትልና “እሰይ! እንኳን አገኘሁህ! አሁን ገና ገበያዚ ሞላ! ለስንት ጊዜ ስፈልግህ ኖሬ ዛሬ ገና ተሳካልኝ፡፡ በል ስለትህን ተሹኹበኝ” ትልና ቡልኮውን እሰውዬው ትኚሻ ላይ ትጥልለታለቜ፡፡

ሰውዬውም ይደነግጥና ‹እንዎ? ምንድነው እሱ – ምን አድርጌልሻለሁ? › በማለት ምክንያቱን ይጠይቃታልፀ እሷም በተመኚሚቜው መሠሚት ነገሩን ኚሥሩ ታስሚዳዋለቜ፡፡ ይሄኔ ያ ሰው ‹ሰይጣንነቱ› ይኚሰትለታልፀ እሱ ሰው እንጂ ሰይጣን እንዳልሆነ በማስሚዳት ጋቢውን ይመልስላትና ወደጉባኀው ተመልሶ ሜማግሌዎቹንም ይቅርታ ጠይቆ ቀድሞ በተነገሹው ዚማስማሚያ ቃላዊ ሠነድ መሠሚት ኚባላንጣው ጋር ይታሚቃል፡፡

ብልሁ መካሪ ሜማግሌ በአንድ ድንጋይ ሁለት ወፍ መምታታ቞ውን ልብ ይሏል፡፡ መግቢያዚ ይህን ይመስላል – አሁን ወደዋናው መስመር ልመልሳቜሁ፡፡

ሰይጣን እንዎት ይታወቃል? ተኚታይ ጋሻ ጃግሬዎቹስ እንዎት ይለያሉ? በጣም ቀላል ነው፡፡ በቅድሚያ ግን እንደመነሻ ኚአሥራ አንዱ ሰይጣናዊ መመሪያዎቜ ሊስቱንና(4ኛውን፣ 7ኛውንና 11ኛውን) ዘጠኙን ሰይጣናዊ ኃጢኣቶቜ ቀጥለን እንመልኚት፡፡

4.  በቀትህ ዚመጣ እንግዳ ካበሳጚህ ያለአንዳቜ ርህራሄ ጭካኔ በተሞላበት ሁኔታ አጾፋውን መልስለት፡፡ (ዐይንን ላጠፋ ዐይንን ማጥፋት ኹሚለው ዚሀሙራቢ ሕግ ጋር ዚሚመሳሰል)

7. ፍላጎቶቜህን ለማሳካት ጥንቆላና መተት ተጠቅመህ ኹሆነ ለዚህ (ሰይጣናዊ) አበርክቶ ዕውቅና ስጥፀ ምሥጋናም አቅርብ፡፡ ይሁንና በጥንቆላና በምትሃት ስኬት ጫፍ ላይ ኚደሚስክ በኋላ ዚበላህበትን ወጪት ሰባሪ ሆነህ ሰይጣንን ብትክድ ያገኘኞውን ሁሉ ታጣለህፀ ዚሰይጣን በሚኚትም ይለይሃል፡፡

11. በዚትኛውም ግዛት ስትጓዝ ስለምንም ነገር ሃሳብ አይግባህፀ በጉዞህ ላይ ዚሚያስ቞ግርህ ሰው ቢገጥምህ በቅድሚያ እንዲተውህ አስጠንቅቀውፀ ካልተወህ ግን ድራሹን አጥፋውፀ ድባቅ ምታው፡፡

 

ዘጠኙ ኃጢኣቶቜ (ሎ቎ኒስቶቜ ሊተላለፏቾው ዚማይገቡ ዚሃይማኖቱ መሥራቜ አንቶን ሌቪ ዚቀመራ቞ው)

  1. ደደብ መሆንና በሌሎቜ ተበልጩ መገኘት (ኃጢኣት ነው!)
  2. እውነትን እንዳመጣጧ በኃይልም በዘዮም በተገኘው ሥልት ሁሉ ኚመጋፈጥ ይልቅ እንደቀሪው ማኅበሚሰብ በአስመሳይነትና በነባር ባህል ለመመሳሰል መሞኹር
  3. ዹኃይል ግብሚ መልስ ዚሚያስፈልጋ቞ውን ነገሮቜ በታጋሜነት ማለፍ
  4. ዹሆነን እንዳልሆነ ወይም ያልሆነን እንደሆነ አድርጎ ራስን ማታለል
  5. ዚራስን ስሜት ኹመኹተል ይልቅ በይሉኝታና በሀፍሚት ታስሮ ዚሌሎቜን ፍላጎት ተቀብሎ በዚዋህነት ኹጎጋው ሕዝብ ጋር መንኹርፈፍ
  6. ወደተፈለገው ግብ ዚሚያደርስ (ማንኛውም ዓይነት) ራዕይና ዓላማ አለመያዝ
  7. ያለፈን ዚሃይማኖትና ዚማኅበሚሰብ ትውፊት መርሣት ሲገባ ያን ማስታወስ
  8. አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ በራስ ስኬት መኩራት ያለመፈለግና ያለመቻል
  9. በሁሉም ዘርፍ ሁሉንም ቀድሞ ለመገኘት በማንኛውም መንገድ ዚተቻለውን ሁሉ ጥሚት አለማድሚግ

 

ሰይጣናዊነትና ተኚታዮቻ቞ው (Satanism and Satanists) በይፋ ቀተ አምልኮ (Church of Satan) አቁመው ሰይጣንን ማምለክ ዚጀመሩበት ዘመን ዚቅርብ ጊዜ ክስተት ቢሆንም ይህ ሃይማኖት በድብቅም ይሁን ሲቻል በግልጜ፣ በሰይጣን ስምም ይሁን በሌሎቜ መጠሪያዎቜ በዚህቜ ዓለም ውስጥ ኅልውናውን ያገኘው ኹሰው ልጆቜ መፈጠር ጋር እንደሚያያዝ መገመት አይኚብድም፡፡ “ሊበሉት ዚፈለጉትን አሞራ ስሙን ይሉታል ጅግራ” እንዲሉ ሆኖ በስያሜ ለሰይጣን ዹቀሹበም ይሁን ዚራቀ በተግባር ግን ሰይጣናዊ ዹሆነ ዚእምነት አካሄድ በዓለማቜን ኹሹጂም ዘመን ጀምሮ በገሃድ ይታይ እንደነበር ለማንም መዝገብ አገላባጭ እንግዳ ነገር አይሆንም፡፡ ባገራቜን ዹቆሌ ባዲገዝና ዚቊሚንትቻ ባህል፣ ‹እነዚህ ባለውቃቢዎቜ ለካንስ ክርስቲያኖቜ ና቞ው› በሚል ዚዋህነት ሰው እንዲኚተላ቞ው ‹ገብርኀልንና አቡዚ ፃዲቁን ዘክሪ፣ ዚሚካኀልን ጠበል ለሊስት ሰባት ጠጪ › ዚሚሉትን አጭበርባሪ ባለአውሊያዎቜ፣ ሌሊት ቅኔ ማኅሌት ላይ ቃለ እግዚአብሔርን በዕዝልና በአራራይ እያንበለበሉ ቀንና ባሳቻ ሥፍራ ግን መጥሐፍ ዚሚገልጡ ደባትርና ታላላቅ ዚቀተ ክርስቲያን ሊቃውንት  በሙሉ ዚአጋንንት ጭፍራዎቜ መሆናቾውንና ይህም ዕኩይ ተግባር ኚጥንት ሲወርድ ሲዋሚድ ዚመጣ ማኅበሚሰብኣዊና ሃይማኖታዊ ክዋኔ እንደሆነ መገንዘብ አይቾግርም – ዚሁለት ጌቶቜ አሜኚር መሆን ዹሚፈልግ ሰው ሁሉ ዚእግዚአብሔር ሣይሆን ዚሰይጣን አሜኚር ነው፡፡ በዚህ መስመር መጓዙ ብዙ ያደክመናልና ባጭሩ እንመለስ፡፡

መጜሐፍ ቅዱስ “ጣፋጭ ፍሬ ኹዛፍ ላይ እንዳለ ያስታውቃል” ይላል፡፡ ዚክርስትና እምነት ቁንጮ ዹሆነው ኢዚሱስ ክርስቶስም እዚህ ዚምናነሳ቞ውን ሰዎቜ “በሥራ቞ው ታውቋ቞ዋላቜሁ” ይለናል፡፡ አዎ፣ ዹማን ማንነት በሥራው ይታወቃል፡፡ አዋዋላቜንም ዹሚናገሹው ብዙ ነው፡፡ ኚነተሚቱ “ጓደኛህን ንገሹኝና ማንነትህን ልንገርህ” ይባላል፡፡ ስለዚህ ኚዚትኛው ወገን እንደሆንን ለመለዚት ቀላሉና ብ቞ኛው መንገድ በሥራቜን ማለትም በዘወትር ተግባራቜን ዹምንገልጠው ዚዕኩይነት ወይም ዚደግነት መገለጫ ምግባራቜን እንጂ ዚአነጋገራቜን ለዛና መስህብ ወይም ዚአለባበሳቜን ማማር ወይም ዚፂማቜን መንዠርገግ አይደሉም፡፡ ዹምንኹተለው ሃይማኖትም ምናልባት ጠቋሚ እንጂ ትክክለኛው ዚመጜደቃቜን ዋስትና አመላካቜ ሊሆን አይቜልም፡፡ በአላህ ስም አንገት እዚቀሉ፣ በእግዚአብሔር ስም ግድያን ጚምሮ ሕዝብ ላይ ሰይጣናዊ ቁማር እዚተጫወቱ፣ ኩነኔ ካልሆነ ጜድቅ ይገኛል ብሎ ማሰብ ሞኝነት ነው፡፡ ሰይጣን ደግሞ ብልጥ ነውፀ ዚምታደርገው ነገር እንጂ ዚምትኚተለው ሃይማኖት ጉዳዩ አይደለምፀ በሥራህ ካኚበርኚው ፓትርያርክም ሁን ኢማምም ሁን ራባይም ሁን ኮርተህ ዚመንግሥቱ ወራሜ ነህፀ እርሱም ዹአንተን ነፍስ ካለተቀናቃኝ ተሚካቢ ነው፡፡ ምሥጢሩ ያለው እዚህ ላይ ነው፡፡ ኹዚህ ውጪ ያለው ነገር ሁሉ ለ‹ምሁራዊ› ፍልስፍናና ለጉንጭ አልፋ ክርክር ፍጆታ ዹሚውል እንቶፈንቶ ነው፡፡

ኹዚህ በተያያዘ ግን በቅድሚያ ዚጋራ መግባባት እንዲኖሚን ዚሚያስልግ ጉዳይ አለ፡፡ እሱም ዕኩይ ስንል ምን ማለታቜን ነው? ደግ ስንልስ? ለሁለቱም መለኪያቜን ምንድነው? በማንስ ዕይታ? ለአንተ ዕኩይ ዹሆነ ነገር ለእኔ ደግ ኹሆነ ዳኛቜን ማን ሊሆን ነው? በአንድ ሀገር ወንጀል ዹሆነ ነገር በሌላ ሀገር ፍቁድ ኹሆነ ዚጋራ መግባቢያው ዹወል ስምምነት እንዎት ሊፈጠር ይቜላል? ነገሩ ቀላል አይደለም፡፡ ብዙ ክርክር ያለው ነገር ነው፡፡

ምሳሌ ወስደን ማዚት እንቜላለን፡፡ በአንዳንድ ዚክርስትና ሃይማኖት ዘርፎቜ ዚተመሳሳይ ፆታዎቜ ወሲባዊ ግንኙነት ኚቀሲስ እስኚ ሊቃነ ጳጳሣት ድሚስ እንደሰደድ እሳት ዹተዛመተ በመሆኑ “ዹኔ ሶዶማዊ መሆን እግዚአብሔርን በ‹ቅንነት› ኹማገልገል ጋር ምን ያገናኘዋል?” በማለት በምድራዊ መንግሥቶቻ቞ው ሕጎቜ ብቻ ሳይሆን በቀኖና ቀተ ክርስቲያንም ውስጥ በቃለ ዐዋዲነት እንዲጜድቅላ቞ው ዚሚታገሉ ‹ዚእግዚአብሔር ቀተሰቊቜ› በብዛት መታዚት ኚጀመሩ ቆይተዋል፡፡ በሌላ በኩል ኚሰይጣን አምላኪዎቜ አካባቢ ለዘብተኛ ዚሚባሉት ይህን እኛ ብዙዎቻቜን በሰይጣናዊነት ዹምንፈርጀውን ዚግብሚ ሶዶም ተግባር ዹሚቃወሙና እንዲያውም ‹ሰው ካልተነኮሰህ አንተ ቀድመህ አትተንኩሳ቞ው› ብለው ዚሚያምኑ “ደጋግ” ሰይጣናውያን አሉ፡፡ በክርስትና ሃይማኖት መስጠት (በብ቞ኝነት ባይሆንም) እንደሚያጞድቅ ይሰበካልፀ በሌላም በኩል በዚሁ ሃይማኖት አንዳንድ ዚተማሩ ተኚታዮቜ ዘንድ መስጠት ሰውን ስለሚያሰንፍ ኚአጜዳቂነቱ ይልቅ አስኮናኝነቱ ይበዛል ዹሚሉ ወገኖቜም አሉ፡፡ ዚክርክሬ አካሄድ ለሁሉም ግልጜ ይሆናል ብዬ አምናለሁ፡፡

ስለዚህ ዕኩይነትና ደግነት እንደቁንጅና ሁሉ ዚተመልካቹን ፍርድ ዚሚጠባበቅ ዋጋው በታሳቢነት ዹሚሰላ ሊሆን ነው ማለት ነው፡፡ ነገሩን ብዙ አናራቅቀውና ሰይጣናዊነትንና ሰይጣን አምላኪነትን እስካሁን ብዙዎቻቜን ዚሚገባንን ያህል አድርገን እንውሰደው፡፡ በነገራቜን ላይ በግርድፍ ግምት አራት ዋና ዋና ቅርንጫፎቜ እንዳለው ኹሚገመተው ዚሰይጣናዊነት እምነት ውስጥ ‹አማፂ ሰይጣናዊነት/Rebel Satanism›ን ያህል ዹኹፋ ዚክፋትና ዹአመፃ ድርጊት ዚሚፈጜም እንደሌለ በዘርፉ ዕውቀት ያላ቞ው ሰዎቜ ይናገራሉ፡፡ በተለይ በአሁኑ ወቅት ዓለምን ኚጜንፍ እስኚ አጜናፍ እያመሳት ያለው አፍራሜ ኃይል (Negative Energy) እንግዲህ ይሄኛው ነው ማለት ነው፡፡ ተኚታይ ዚጥፋት ኃይሎቹም በሀገራቱ መንግሥታትና በኅቡዕም ይሁን በግልጜ በሚንቀሳቀሱ ተቃዋሚ ቡድኖቜ ውስጥ ዹተሰገሰጉ በደም ዚሚነግዱ ጚካኝ ዜጎቜ ና቞ው፡፡ ዚነሱ ጭካኔ በጹለማው ንጉሥ በዲያብሎስ ዘንድ ዚሚያሞልምና ዚሚያሟም ድንቅ ሥራ ነው፡፡ በገደሉ ቁጥር ደስታ቞ው ይበዛልፀ ባሰቃዩ ቁጥር ዚመንፈስ መነቃቃትን ያገኛሉ፡፡ ዚደግነት ምግባር ዚሚያስኚፋ቞ው፣ ዚክፋት ሥራ ጮቀ እሚያስሚግጣ቞ው ዚተንኮልና ሞር አምባሳደሮቜ ና቞ው፡፡ በግዛታ቞ውና በዘመነ ሥልጣና቞ው ዹተገኘን ምሥኪኖቜ ግን እናሳዝናለን – ኚልባዊ በስማምና አቡነ ዘበሰማያት ሌላ ምንም ጩር ዹሌለን ድሃ ወገኖቜ ይህ ዘመነ ሰልቢያኖስ ክፍላቜን አይደለም፡፡

ጉንጭ አልፋ ክርክራቜንን ትተናል፡፡ ክፉ ማለት ሆን ብሎና አለ አንዳቜ ምክንያት – ለሥጋዊ ጥቅምና ፍላጎቱ ሲል ዚሚገድል፣ ዚሚያሥር፣ ዚሚያሰቃይ፣ ዚሚጠላ፣ ዚሚያዳላ፣ ሆን ብሎ ዚሚጎዳ፣ ዚማይስማማ፣ ዚሚያስርብ፣ ዚሚያስጠማ፣ ዚሚያሰድድ፣ ዚሚያሳድድ፣ ዚሚኚፋፍል፣  
 ነው ብለን ለጊዜው እንስማማ – እንደወያኔዎቜ፡፡ እነዚህንና ሌሎቜ ብዙዎቻቜን በክፉ ሥራነት ዚምንስማማባ቞ውን ዚክፋተኝነት ድርጊቶቜ ዚሚፈጜም ዐወቀውም አላወቀውም – ወደ ቀተ ሣጥናኀል ሄዶ ጾለዹ አልጾለዹ – ዚቀተ ሰይጣን ተኚታይ (ሎ቎ኒስት) ነው፡፡ እርግጥ ነው ኚሎ቎ኒስቶቜም ‹ዘመናዊ ሎ቎ኒስቶቜ(Modern Satanists)› ዚሚባሉት በስም ብቻ ሣይሆን በተግባርም ‹ክርስቲያን ነን› ኹሚሉ አንዳንድ አስመሳይ ወገኖቜ ጋር ዚተቀራሚበ እንዲያውም ዚተሻለ ባሕርይና አመለካኚት እንዳላ቞ው በዘወርዋራም ቢሆን ኹፍ ሲል ዐይተናል፡፡ ትልቁ ቁም ነገር ስማዊው ዚዚሃይማኖቶቻቜን መጠሪያ ሳይሆን ዋና ዚማንነት መገለጫቜን ተግባራቜን ነው፡፡ እናም እንደኔ እንደኔ ክፉኛ ግራ ኚመጋባቱ ዚተነሣ በሰይጣን ግዛት ሥር አድሮ ነገር ግና መልካም ሥራ ዚሚሠራ ሰው በእግዚአብሔር ግዛት ሥር ሆኖ በማወቅ ክፉ ሥራ ኚሚሠራ ሰው ያነሰ ዋጋ ያገኛል ብዬ አልገምትም፡፡ ልብንና ኩላሊትን ዹሚመሹምር ዚሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር ዋጋቜንን ዹሚተምነውና ዚዚመክሊታቜንን ዹሚሰጠን በሰው – ሠራሜ ዚልዩነቶቜ ጎራ ተመሥርቶ ሳይሆን በግብር በምናሳዚው መልካም ሥራቜን ላይ ተመሥርቶ መሆኑን አምናለሁ፡፡ ዹሆነው ቢሆን ግን “ዕብድ ቢጚምት እስኚ ዕኩለ ቀን ነው” እንዲሉ ነውና በተለይ ሰይጣናዊነትን በምንም መንገድ ዚማላበሚታታ መሆኔን በዚህ አጋጣሚ ላሰምርበት እወዳለሁ፡፡

ዓለማቜንን ዚሠይጣን መፈንጫ ለማድሚግ ዹተጀመሹው እንቅስቃሎ እጅግ በጣም ዚቆዬ እንደሆነ ይነገራል፡፡ እንደዚህ ዘመን ግን ሰይጣናዊነት በምልዓት ዚተገለጠበት ዘመን ታይቶ አይታወቅም ነው ዚሚባለው፡፡ በተለይ ዹፊልምና ዹሙዚቃው ኢንዱስትሪ ግዘፍ ነስቶ እንዲህ ጫፍ በደሚስ ሁኔታ ዹዓለም ወጣት ዜጎቜን መጫወቻ ማድሚግ ኹተጀመሹ ኹ19ኛው መቶ ክፍለ ዘመን አጋማሜ ወዲህ ዚእግዚአብሔር ስም እንዳይጠራ እንኳን እዬተደሚገ ያለው ሰፊ ዘመቻ በታላቅነቱ ወደር ዚሚገኝለት አልሆነም – እውነቱን ለመናገር ዚእግዚአብሔርን ስም መጥራት በርሱም ማመን ፋራና ኋላ ቀር እያስባለ፣ ብዙዎቜንም እስኚማሣፈር በደሹሰ ሁኔታ ኚእውነተኛው መንገድ እያሰናኚለ ዚምንገኝበት ጊዜ ላይ ደርሰናል፡፡ በተቃራኒው ግን ዱሮ ያሣፍር ዹነበሹ ጠንቋይና ደብተራ ቀት እዚሄዱ መጎናበስና ዚሰዎቜን ጫማ መላስ ዛሬ ዛሬ ዚሚያኮራ ዹዘመኑ ፋሜን ሆኗል፡፡ ጎሚቀትህን፣ ጓደኛህን፣ ሀብታምን፣ ታማሚን፣ ምቀኛ ድሃን  ተመልኚትና ይህ ዹምልህ ነገር እውነት ሀሰትነቱን አጢን፡፡ ዚጠፋንበት ዘመን ላይ እንደምንገኝ አትጠራጠር፡፡ ኹሞላ ጎደል ሁሉም ባለፀጋና ዹተደላደለ ኑሮ ዹሚኖር አብዛኛው ሰው አንድም ዚሰይጣን አምላኪ ነውፀ አንድም በተለያዩ ወንጀሎቜ ዚሚታማ ነው – ሁሉም ግን ዚሰይጣናዊነት መገለጫ በመሆኑ ሰውዬው ያው ሎ቎ኒስት ነው – እንደአካሄድ ቅዱስ ሰይጣንና እርኩስ መልአክ ዹሉም – ምርጫው አንድና አንድ ብቻ ነውፀ እግዚአብሔር ወይ ሰይጣን – ብርሃን ወይ ጚለማ፡፡ ዹምልህ ነገር ዹምቀኛ ወሬ እንዳይመስልህ፡፡ አንተም ብልጥ ኹሆንክ ሰይጣን ዹመሆንና እንደነሱ ዹመክበር ቩርቃቃ ዕድል አለህፀ አለበለዚያ ለፍተህና ጥሚህ ግሹህ በወዝህ መኖር፡፡ በበኩሌ ሰይጣን ዹመሆን ዕድሉ ነበሚኝፀአለኝም፡፡ ግን አልተጠቀምኩበትምፀወደፊትም ዚምጠቀምበት አይመስለኝም፡፡ ስለወደፊት እርግጠኛ መሆን ስለማይቻል ነው ዚተጠራጠርኩ ዚመሰልኩት፡፡ እንጂ ዚሰይጣን ሀብት ምኑ ሊያስቀና! በአፍንጫዚ ይውጣ!

ኹፍ ሲል እንደተገለጞው ወጣቱን ማግኘት ዚሚቻለው በአብዛኛው በሙዚቃና በፊልም እነዚህንም ዋነኛ መደላድል በሚያደርገው በወሲብ አማካኝነት ነው፡፡ እነዚህን ነገሮቜ ለማሣካት ደግሞ ዚገንዘብ አስፈላጊነት አማራጭ ዚለውም፡፡ ለዚህም ነው መጜሐፉ “ገንዘብ ዚኃጢኣት ምንጭ ናት” ዚሚለው፡፡ በእያንዳንዱ ሀብት በስተጀርባ ወንጀል ስለመኖሩ በተደጋጋሚ ዚሚወሳውም ዚገንዘብን ዚነፍስ አማሣኝነት አጉልቶ ለማሳዚት ነው፡፡ አሁን በዘመናቜን ኚፈጣሪ ይልቅ ቀተ አምልኮ አልቆመለትም ጜላትም አልተበጀለትም እንጂ ገንዘብ እስኚመመለክ ዹደሹሰው ሰው ራሱ በሠራው ዚምድር ንዋይ ፈጣሪን መለወጡን ዚሚያሳይ ዚዝቅጠት ምልክት ነው፡፡ በዚህ ዘመን እጅግ ብዙ ሰዎቜ ሁሉንም ዚሃይማኖትና ዚሞራል ድንበሮቜ ጥሰው አቅላቾውን በመሳት ገንዘብን ዚሚያሳድዱት ዹዓለም ብልጭልጭ ነገሮቜ ካለገንዘብ እንዲሁ በምኞት ብቻ ሊገኙ ስለማይቜሉ ነው፡፡ እዚህ ላይ ምርጫው ሁለት ነው – ኚጀናማ ኅሊና ጋር በእውነተኛው ገቢ በድህነት እዚኖሩ መቾገር ወይም በሰይጣናዊ ቀድዶ ሕክምና ኅሊናን ኚጭንቅላት አውጥቶ በ‹ጅብ ኹሚበላህ በልተኾው ተቀደስ› ዘይቀ በተገኘው መንገድ ሁሉ ለቁሣዊ ሕይወት ብልፅግና መጣር፡፡ በዚህኛው አቅጣጫ ለሚመራ ሰው ገንዘብ እስካስገኘ ድሚስ ማንኛውም እንቅስቃሎ በሕግ ቢኚለኚልም በተግባር ዹተፈቀደና ያልተኚለኚለ ያህል ዹሚቆጠር ነው፡፡

መንግሥታዊ ሥርዓቶቜም ዹዚሁ ዚንቅዘት ሥርዓት አባላት በመሆናቾው እነሱም ዚበኩላ቞ውን ይሞስናሉፀ ኚቢጀዎቻ቞ውም ጋር ይተባበራሉፀ ያስተባብራሉ፡፡ ዚማይሞስን ዚነሱ ፀር መስሎ ስለሚታያ቞ው ባገኙት ዘዮ ሁሉ ያጠፉታል – በ‹ዚምዬን እኚክ ወዳብዬ› ሥልት ሙሰኛ ነው ብለውም ዘብጥያ ሊያወርዱትና በፈጠራ ክስ ሊያሰፈርዱበትም ይቜላሉ፡፡ ስለሆነም ሞሳኝና አስሞሳኝ፣ በራሱ አንጡራ ገቢ ዚማይኖር፣ ያልተፈቀደለትን ማንኛውንም ነገር ኹሰው ዚሚቀማ፣ ሥልጣኑን ለመጹቆኛ እንጂ ባግባቡ ዚማይጠቀም፣ ሕዝብን በሥልጣኑ ዚሚበድልና ዚሚያጉላላ ሁሉ ዚሰይጣን ወገን ነው፡፡ በዚህም ዚሰይጣን ወገን ይታወቃል፡፡

ወደሰይጣናዊ ተቋማትና አመራሮቻ቞ው እንመለስ፡፡ ብዙዎቹ ምናልባትም ሁሉም ዹነዚህ ዓለም አቀፍ ታላላቅ ተቋማት ባለቀቶቜ በኢኒሌሜን ፒራሚዳዊ ዹደሹጃ ሠንጠሚዥ ኹፍተኛውን ዲግሪ በያዙ ዹዚህኛው ወይም ዚዚያኛው ምሥጢራዊ ሰይጣናዊ ድርጅት አባላት ና቞ው፡፡ (ለጠቅላላ ዕውቀት፣ ዚቀተ ሣጥናኀል አመራር መዋቅር ዲግሪ ኹ1-5 ሲሆን ‘the Skull and Bones’ን ዚመሳሰሉ ኚዓለማቜን ሀብትና ሥልጣን ጀርባ ዹሚገኙና ወደጥልቁ ዚጥፋት ባህርም እያዳፉን ዚሚገኙት ዚምሥጢራዊ ድርጅቶቜ ዲግሪ ደግሞ ኹ1-33 እንደሚደርስ ይነገራል፡፡ ይህ ዲግሪ ለነሱ እንደማዕሚግ ዹሚቆጠር ነው – በልፋት(በጥፋት?) ዹሚገኝ!)

ዚሚደነግጥ እንዳይኖርብኝ እሰጋለሁ እንጂ በአሁኑ ወቅት ሎተኒስቶቜ ሁሉንም ዹዓለም ነገር ተቆጣጥሚዋል፡፡ ዚቀራ቞ው ያለ አይመስልም፡፡ አንተንም አንቺንም እኔንም ተቆጣጥሚውናል፡፡ በምትበላው፣ በምትጠጣው፣ በምትለብሰው፣ በምትጓጓዝበት  ይመጡብሃል – በዕቃዎቜ ላይ በግልጥም ይሁን በሥውር በሚለጥፉብህ ዹ666 ምልክታ቞ው ብቻ እንዳይመስልህ – እስትንፋስህን ሳይቀር ተቆጣጥሚውታል እያልኩህ ነው ወንድሜ (ፈገግ በል አስኪ፡- ሜንት ቀት ገብተህ ወደዋናው ጉዳይ ኚመግባትህ በፊት በእንትንህ ሙዚቃ ስን቎ እንደተዝናናህ ሳይቀር እነሱ ኹፈለጉ ያውቁታል፡፡ አዲዮስ ‹privacy›፣ ገባህ? አትታዘበኝ – አዲስ ነገር ዚለም፡፡ )

በተለይ ኢትዮጵያን በመሰሉ ድሃ ሀገሮቜ ውስጥ ዹሚገኘውን ዚድሃ ገበሬ ማሣ በማዳበሪያ አፈር ድሜ አብልተውታልፀ በኬሚካላ቞ው ዚገበሬውን መተዳደሪያ ዚተፈጥሮ ማዕድን ሲያቃጥሉት በውድ ኹሚገዛው ዚነሱ ማዳበሪያ ውጪ አፈሩ ዘር ማብቀሉን ተወ – ኬሚካሉን ልግዛ ሲል እነጉናና አምባሰልን በመሰሉ ዹሀገር ውስጥ ወያኔያዊ ሌሪኮቻ቞ው አማካኝነት ዋጋውን ሰማይ ሰቀሉትፀ እኛንም ገበሬውንም ለቜግር ዳሚጉንና ሁላቜንም ኀሎሄ እንል ጀመር፡፡ በግብርናውም ሆነ በኢንዱስትሪውና በፖለቲካው መስክ ኚነሱ ቁጥጥር እንዳትወጣ ዚማያደርጉት ነገር ዚለም፡፡ ድመት ዚገደለቻትን ዐይጥ እስክትበላት ድሚስ እንደምትጫወትባት ሁሉ እነዚህ ጥቂት ዚአጋንንት ውላጆቜ እንዳሳሁርታ በቅጜበቶቜ እዚተራባ ዚሰባት ቢሊዮንን ጉበን በቅርቡ ያለፈውን ዹዓለም ሕዝብ ጢባጢቀ እዚተጫወቱበት ና቞ው፡፡ በቁራጭ አሞሌ ጹው በሬ ወደመታሚጃው እንደሚሄድ እነዚህ ገብጋቊቜ ዹዓለምን ሀብትና ፖለቲካ በቀጥታና በእጅ አዙር ተቆጣጥሚው ወደ አጠቃላይ ውድመት እዚመሩን ና቞ው፡፡ በዚህም ሰይጣኖቜን ታውቃለህ!

ዚትም ሂድ ዚትም ግባ ቀተ ክርስቲያንን ሳይቀር በአለቃቾው ዚሰይጣን መንፈስ ተቆጣጥሚዋል – ኢትዮጵያ ውስጥ ለምሳሌ እስኚቅርብ ሩቅ ድሚስ ዋልድባ ገዳምን ሰይጣን እምብዝም አይደፍርም ነበር (ይባላል)ፀ አሁን ግን ገዳሟ መንፈላሰሻ቞ው ሆናለቜ – ዚነደብሚ ሊባኖስና ዚሌሎቜ ደብሚዎቜ ነገር ተኚድኖ ይብሰል፡፡ እነዚህ ገዳማትና አድባራት ዋና መሥፈሪያ ቆጣ቞ው ና቞ውፀ ጞሎቱ ዚማያርገው፣ ስብኚቱ ዹደነደነ ልብን አሟምቶ ኚኃጢኣት መንገድ ዚማይመልሰው፣ ሕዝበ ክርስቲያን ዚዳነ እዚመሰለው ሃይማኖቱን እንደሞሚዝ ዚሚቀያይሚው ኹዚህ ዚተነሣ ነው – ሀሰት ኚተናገርኩ 
 ዳሩ አይማልም ለኬ፡፡ ዹምለው ግን እውነ቎ን ነው!

ዘመኑ ዚጭንቀትና ዚጥበት ነው፡፡ መዳን በዚህ ወይ በዚያ አለ ዚሚባልበት ድኅነት ግን ዚሌለቜበት እጅግ አስጚናቂ ዘመን ላይ ልንገኝ ዚቻልነው አእምሮኣቜንን ዚስንግ በያዙን ሎ቎ኒስት መሪዎቻቜን አማካይነት ራሱ ዲያቢሎስ ዚፊጥኝ ስላሰሚን ነውፀ አሳዳጃቜን ሰይጣን በምንሄድበት ቊታ ሁሉ ቀድሞ ይጠብቀናል፡፡ እሥሚኞቹ ደግሞ በጎቹ ብቻ ሣንሆን እሚኞቻቜንም ና቞ው፡፡ አዲስ አበባን ተመልኚት፡፡ በዲኀክስና በቪታራ  ዹሚዝመነመነውን ዚደብር አለቃና ዹሀገሹ ስብኚት ባለሥልጣን ካህን ስታይ፣ ዚዚአጥቢያ አብያተ ክርስቲያን ታዋቂ ቀሣውስትና መዘምራን ወሰባኪያን በም቟ት አብጠው እንደ እምቧይ ሊፈርጡ ተቃርበው ስታይ ያቺ ካላት ሳይሆን ያላትን ኚመቀነቷ ፈትታ ወደ ሙዳዚ ምጜዋት ዚምትጚምር ሎት በዐይነ ልቩናህ ትታይሃለቜ፡፡ እኛ እዚኮሰመንን እነሱ እዚተነፉ፣ እኛ እዚደኞዚን እነሱ እዚኚበሩ፣ እኛ እዚፆምን እነሱ እዚፈሰኩ፣ 
 መኖር ተብሎ አለሃይማኖትና አለመሪ ዚአጋንንት ወጀብ እያላጋን ተገትሚን አለን፡፡ ዘመኑ ቀርቧል ዹምንለው እንግዲህ ኹነዚህ ነገሮቜ አንጻርም ነው፡፡ ሁሉም ዚውሞት ነው – ዚታይታ፡፡ ይህን ግን አስብ፡- ‹ዚእግዚአብሔርና ዚሰይጣን ሰዎቜ በሥራ቞ው ይታወቃሉፀ ዚታይታ ፆምና ስግደት ወይም ዚፈሪሳውያንና ሰዱቃውያን ዓይነቱ ዚአለባበስና ዹአነጋገር ላህይ ሳይሆን – እምነት፣ ሥራና ፍቅር ዹሰውን ምግባር ይገልጣሉ፡፡› በቃ፡፡

ዚሌሎቜን ዚእምነት ቀቶቜም ተቆጣጥሚዋል፡፡ ሚዲያውም በነሱው ቁጥጥር ሥር ነው፡፡ እነሱ ዚሚፈልጉት ዜናም ሆነ ሀተታ ይነገራልፀ ሌላውና ኚነሱ ፍላጎት ውጪ ዹሆነው ግን ይታፈናል፡፡ ዚዚሀገራቱ መሪዎቜ ሎ቎ኒስት ካልሆኑ ኚሥልጣን ዚሚወርዱበት መንገድ ይጠናና ተግባራዊ ይደሚጋልፀ ምክንያቱም እንደኃያላኑ መንግሥታት መሪዎቜ ሌሎቹም ሎ቎ኒስቶቜ ካልሆኑ እንደልብ አይታዘዟ቞ውም – ሰይጣንና መልአክ – እርኩስና ቅዱስ ውሃና ዘይት ና቞ውና፡፡ ዚሆሊውድንና ዚሌሎቜ -ውዶቜን ፊልሞቜና ሙዚቃዎቜ ቃኙፀ ኹሞላ ጎደል ሁሉም ማለት በሚቻል ሁኔታ አገልግሎታ቞ው በሰይጣናዊው አዲሱ ዹዓለም ሥርዓት [The New World Order] መሠሚት ዹተቃኘ ነው፡፡ ለነሱ ዚማይስማማ ይወገዛል – ተጠርጎ ይጣላልምፀ ለነሱ ዚሚስማማ ጚካኝና አውሬም ቢሆን እንደጫጩት ጉያ ውስጥ ይታቀፋል(ሳዑዲንና ባሕሬይንን ያስቧል)ፀ (ዚቬንዞላ ሕዝብ አሜሪካ ዚምትፈልገውን ካፒሪሌን ትቶ ማዱሮን መምሚጡ ስህተት ነውፀ እና አሜሪካ ዚምርጫውን ውጀት አትቀበልም፡፡ ዚኢትዮጵያው ዹ97 ምርጫ ግን – ዌል – እንደዎሞክራሲያዊ ተሞክሮ ስለሚቆጠር – ተቃዋሚ በዝሚራ ቢያሞንፍም – እርግጥ ነው – ወያኔ አሾንፏል ማለት ይቻላል፡፡ ተቃዋሚዎቜ ዚተሰጣ቞ውን ወንበር መቀበልና በመናጆነት በወያኔ ፓርላማ በሚት ገብተው ማንቀላፋት ነበሚባ቞ው፡፡ 
 ዚጉዶቜ ምድር፣ ዚምፀት ዓለም
 “ሥራ ለሠሪው እሟህ ላጣሪው ”ይብላኝ ለንጹሑ ሰላማዊ ሕዝብ! ዐይጥ በበላ ዳዋ ተመታ 


በነገራቜን ላይ ሁለት ወጣቶቜ ብቻ አሜሪካውያንን በ‹ጊር ሜዳ ውሎ›ና በፕሮፓጋንዳ እንዲህ ‹ሜንት በሜንት› ያደሚጉ፣ ዹዓለምን ሚዲያ በመሪና በሰበር ዜናነት ኚዳር እዳር ያጥለቀለቁ፣ ፕሬዝደንት ኊባማን ሣይቀር እንቅልፍ አሳጥተው ያስጚነቁና ዕንባ በዕንባ ያስደሚጉ አሥርና አሥራ አምስት ቢሆኑ ምን ያሳዩ ይሆን? በዛሬዋ ቀን እያዘንኩም ቢሆን ሁለት ዜናዎቜ ፈገግ አድርገውኛል፡፡ አንደኛው እነኢራንንና ሰሜን ኮሪያን ፌሜታ በፌሜታ ዚሚያደርገው ምናልባትም በሣቅ ዚሚያፈነዳው ዚቊስተኑ ክስተት ሲሆን ሁለተኛው ያ ሙሻራፍ ዚሚባል ገልቱ ሰውዬ በሀገር ክህደትና በሌሎቜ ወንጀሎቜ ዘብጥያ ሊወርድ ኹሞቀ ዚስደት ኑሮው መመለሱና ዛሬ በፖሊስ መያዙ ናቾው – ዚሥልጣን ፍቅር አነሁልሎት እውነቱ ተሞፈነበትና ጉድ ተሠራ፡፡ በጊዜያቜን ብዙ ነገሮቜ ኹመግሹም እያለፉ እንደጅል በሞኝነት ማሣቅ ይዘዋል፡፡ ፈገግ ብትሰኙልኝ አንድ አስቂኝ ታሪክ እዚቜ ላይ ባጭሩ ላስታውሳቜሁ፡፡(ዚአሜሪካው ትዕይንት ግን ሆሊውድ በቊስተን ዚቀሚጻ ልምምድ እያደሚገ አልመሰላቜሁም?)

በዱሮ ጊዜ ነው አሉ፡፡ ዚኢትዮጵያ መንግሥት አንድ ዹጩር ቡድን ወደ አንድ ጫካ ይልካል፡፡ ያስ቞ገሚ አስ቞ግሮ ነበርና፡፡ ኚጊርነቱ መልስ አንድ ሰውዬ ዹጩር አዛዡን ጠጋ ይልና እንደሚኚተለው ይጠይቀዋል፡፡

ጠያቂ፡- ውጊያው እንዎት ነበር? በቀላሉ ቀናቜሁ ወይንስ ጉዳት ደሚሰባቜሁ?

አዛዥ፡- ኧሹ ምኑ ይወራል! በጣም ኃይለኛ ጊርነት ነበርፀ ያልጠበቅነው ብዙ ጉዳት ደሚሰብን 

ጠያቂ፡- እንዎ? ብዙ ዚጠላት ኃይል ነበር እንዎ ዚገጠማቜሁ? ማለቮ ኚእናንተ ዚሚበልጥ 

አዛዥ፡- አሄሄ
 እንደሱማ ቢሆን በማን ዕድላቜንፀ ዹገጠመን አንድ ሰው ብቻ ሆኖ ውር ውር እያለና         እዚተሜሎኚለኚ ፈጀን እንጂ፡፡ በስንት መስዋዕትነት መሰለህ መጚሚሻ ላይ ዹገደልነው 


 

ኢትዮጵያቜን በሰይጣን ግዛት ኚገባቜ ቆይታለቜ፡፡ በፊትም ግማሜ እግር በሰይጣን ግዛት ግማሜ እግር በእግዜር ግዛት ውስጥ በጹለማና በብርሃን በሚመላለስ ዹአገዛዝ ሥርዓት ውስጥ ነበሚቜ፡፡ እዚቆዬ ደግሞ በለዬለት ሁኔታ እዚያው እጚለማው ግዛት ገባቜና አሁንም ድሚስ በዚያው አለቜ፡፡ እግዚአብሔር ይርዳት፡፡

በእስልምና ስም እዚታዬ ያለውም ዹሚዘገንን ነው፡፡ ሰሞኑን ኚድሚ ገፆቜ ስለአንዲት ኢትዮጵያዊት ልጃቜን ያነበብኩት ሰቅጣጭ ታሪክ ወደውስጀ አስለቅሶኛል – ወደ ውጪ ዚማፈስሰው ዕንባ ዚለኝምፀ ለጊዜው ጚርሻለሁ፡፡ ይህቜ ልጅ እንደብዙዎቹ ኚርታታ ወገኖቻቜን ሁሉ ያልፍልኛል ብላ ወደዐሚብ ሀገር ትሄዳለቜ፡፡ ሊርያ ውስጥ ገብታ ሥራ ትይዛለቜ፡፡ ነገር ግን ‹አንበሣን ፈርቌ ዛፍ ላይ ብወጣ ነብር ጠበቀኝ› እንዲሉ ሀገሯ ያስወጣት ቜግር መልኩን ቀይሮ ሊርያ ላይ ጠበቃት – ጊርነት፡፡ ኚርሀብ ስትሞሜ ጊርነት አፉን ኚፍቶ ጠበቃት፡፡ በዚህ ዚርስ በርስ ውጊያ ሰበብ ቀጣሪዎቿ ቀቱን ጥለውላት ወደዉጭ ይሰደዳሉ፡፡ ዝርዝሩን ኚነዚያው ድሚ ገፆቜ አንብቡ፡፡

ሳላነሳው ማለፍ ዹማልፈልገው ግን ለዚህ መጣጥፍ መነሻ ዹሆነኝ ዚዚህቜ ልጅ ስቃይ ነው፡፡ ይህቜ ልጅ ደማስቆስ ዚመሬት ለመሬት ዚውስጠኛ ክፍል ውስጥ በመሾጉ አሞባሪዎቜ እጅ ትወድቃለቜ፡፡ በነዚህ ዚእስላም አክራሪ ሰይጣኖቜ ቁጥጥር ኚገባቜ በኋላ ዚምታዚው አበሳ በቃላት ዚሚገለጜ አይደለም፡፡ እግዚአብሔር ዚሰይጣኑን ዚመለስ ዜናዊን ነፍስ ተገቢ ዋጋዋን ይስጣትና በሱ ዹተንሾዋሹሹና በዘሚኝነት ዹበኹተ አገዛዝ ምክንያት ወደዉጭ ዚሚሰደዱ ወገኖቻቜን ምን ዓይነት መኚራና ስቃይ እዚደሚሰባ቞ው እንደሚገኝ ይህቜ ልጅ አብነት ናት፡፡ በብዙ ሺዎቜ ዚሚገመቱ ወገኖቻቜንም በዚህ ዓይነት አሰቃቂ ሁኔታ እንደሚኖሩ ዚሚታወቅ ነው፡፡ ይህ ለቀት ቀጋ ለውጭ አልጋ ዹሆነ ሥርዓት በቶሎ ካልተወገደ በሀገራቜን ምን ያህል ውድመት እዚደሚሰ እንዳለና ወደፊትም ዚሚመጣብን መኚራ በዚህቜ ልጅ አማካይነት ቁልጭ ብሎ ይታያልና ወደዚኅሊናቜን ተመልሰን ለጋራ ጉዳያቜን በጋራ እንድናስብ ይህ ዓይነቱ አስኚፊው ተሞክሮኣቜን ያስተምሚን፡፡ በፈጠሹን ይሁንብን!

አሞባሪዎቹ ይህቜን ልጅ በሚስቶቻ቞ው ፊት ሳይቀር ይደፍሯታልፀ ሌሎቜን በኮሚንቲ እንድትጠብስ ያደርጓታልፀ ሜንታ቞ውን እንድትጠጣ – ዚርሷንም ሜንት ሌሎቜን እንድታጠጣ ያደርጓታልፀ ሬሣ መሀል እንድታድርና አእምሮዋን ስታ ወደአውሬነትም ተለውጣ ለአጥፍቶ መጥፋት ተልእኮ ፈቃደኛ እንድትሆን ያስገድዷታል፡፡ ዝርዝሩ ብዙ ነው፡፡ ኢትዮጵያዊ ነኝ ዹሚል ዚዚህቜን ልጅ ስቃይ ያላነበበ ኚአንዱ ድሚ ገጜ ቢያነብ ደስ ይለኛል (በዚህ በኩል ልምዱ ያላቜሁ ዚዘሀበሻ ድሚገፅ ሰዎቜ እባካቜሁን እዚህቜ ቊታ ላይ ዚዚያን ጜሑፍ አድራሻ አጣቅሱት – እኔ ያነበብኩት በኢትዮሚዲያ ላይ ነውፀ ርዕሱ ‹ኢትዮጵያዊቷ በሊርያ ያሳለፈቜውን ስቃይ › ዹሚል ነው – ኚአዲስ አድማስ ጋዜጣ ነው ዚወሰዱት)፡፡ ዚእርሷ ስቃይ ዹኛ ስቃይ ነው፡፡ ይህቜ ልጅ ዹኔንም ምስል ዚምታሳይ ሎት ክርስቶስ ናት፡፡ ዹገማና ዚሻገተው ማኅበራዊና ፖለቲካዊ ሥርዓታቜን ነፀብራቅ ናትፀ ዚመለስ ራዕይ ውጀት ያስገኘልን ድል መገለጫ ዹኅሊና ጞጞታቜንና ዚጋራ ቁጭታቜንም መንስኀ ናት፡፡ ያንዳቜን ቁስል ላንዳቜን ካልተሰማን ኢትዮጵያውያን ብቻ ሳንሆን ሰዎቜም አይደለንም ማለት ነውፀ ያለአንዳቜ ቅድመ ሁኔታ አንዳቜን ለአንዳቜን እንተዛዘን፡፡ በነገራቜን ላይ ይህቜ ልጅ ፈጣሪ በሰዎቜ አማካይነት ሚድቷት ኚዚያ ዹቁም መቃብር ተርፋ አሁን በሕይወት አለቜ፡፡

እንግዲህ ሰይጣን ማለት ኹፍ ሲል እንደተመለኚትነው ነው – ዕልቂትና ትርምስ ዚሚወድ፡፡ በሊርያ፣ በኢራቅ፣ በአፍጋኒስታን፣ በፓኪስታን፣ በሕንድ፣ በሶማሊያ፣ በግብጜ፣ በፍልስጥኀም፣ በበርማ፣ በኢንዶኔዥያ፣ በአሜሪካዎቜ፣ በማሊ፣ በሎንትራል አፍሪካ ‹ሪፓፕሊክ›፣ በጊኒ፣ 
 ሠይፉን መዝዞ ሕዝበ አዳምን እያንቆራጠጠ ዹሚገኘው ሰይጣን በሰዎቜ ተመስሎ ነው – (በነገራቜን ላይ ሰይጣንም ሆነ እግዚአብሔር – በጹለማና በብርሃን በሚመሰል ዚመንፈስ ኃይል እንጂ ዚራሳ቞ው ቁሣዊ መገለጫ እንደሌላ቞ው ዚታወቀ ነው፡፡) ቊስተን ላይ ዚፈነዱት ሁለት ቊምቊቜ ዚሰይጣን ና቞ውፀ ኢራቅ ውስጥ በዹቀኑ ዚሚፈነዱ ቊምቊቜና ዚአጥፍቶ ጠፊ ተልእኮዎቜ ኚሰይጣን ዚሚላኩ ና቞ው፡፡ ሶማሊያ ውስጥ ዚሚፈነዱ ቊምቊቜ ዚሰይጣን ና቞ው፡፡ እስላም እማሬያዊ ትርጉሙ ‹ሰላም› ሆኖ ሳለ ሰይጣን አእምሮኣ቞ውን ዚሠሚራ቞ው ሰዎቜ በዚህ ሰላምን በሚሰብክ ሃይማኖት ሜፋን ስም ገብተው ዓለምን ወዎት እያቀጣጯት እንደሆነ ልብ እንበል፡፡ ዚዕብድ ገላጋይ ድንጋይ እንደሚያቀብል ሁሉ በሌላው ጫፍ ያሉ ዚሰይጣን ሎሌዎቜና ደንገጡሮቜም ዚጠቡን አድማስ ኚማጥበብ ይልቅ እዬለጠጡና ነገር እዚተነኮሱ አለይዞታ቞ውም በሰው ግዛት ጥልቅ እያሉ በሚያቀጣጥሉት ዚ‹አሞባሪነትና ተሞባሪነት› አሾናፊ ዹሌለው ጊርነት ውስጥ ዚስንቶቜ ንጹሓን ዜጎቜ ሕይወት በዹቀኑ እንደሚሚግፍ እናስተውል፡፡ አስቂኝ ቀልድ – አሞባሪነትን በአሞባሪነት ለማሾነፍ ዹመሞኹር ልዩ ዹ21ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ትራጂኮሜዲ ድራማ፡፡ በሰዎቜ ዕልቂት ሰዎቜ ዚሚጚፍሩበት አሣዛኝ ተውኔት፡፡ ዓሣሞቜና አጋሰሶቜ – ማነው – ዝኆኖቜ ሲጣሉ ሣሮቜ ዚሚሚጋገጡበት ክፉ ዘመን፡፡ ምን ይሻለናል? ጊዜው አያስፈራም? ዹኔ ስሜት ድብልቅ ነው – ያስፈራል ፀ አያስፈራምም፡፡

ዚእንቅስቃሎውን ስም አልቃኢዳም እንበለው አልሻባብ፣ አል ኑስራም እንበለው አል ዛዋሪ – ሃይማኖቱ እስልምናም ይሁን ክርስትና ቡድሂዝምም ይባል አይሁድ ተግባሩ ሰዎቜን መጚሚስ ኹሆነ ያው ሰይጣን ነው፡፡ ሰይጣናዊነት ሰብኣዊነት ዹሌለው በግድያ እንድትዝናና ዚሚያደርግ ዚጭካኔ አምልኮት ነው፡፡ በሰው ስቃይ ዚሚደሰት ሁሉ ሰይጣን ነው፡፡ ዹተቀደሰ ግድያ ዚለም፡፡ ግድያ በማንም ይሁን በማን፣ ማንም ላይና ለምንም ዓይነት ዓላማ  ይፈጾም አስኚፊ ነገር ነውፀ አስተማሪነትም ዚለውም፡፡ ዹሞተም አልተማሚምፀ ዹተመለኹተም ኅሊናውን በሚያሰቃይ ቁስል አነፈሹቀ እንጂ ትምህርት አልቀሰመም፡፡ በተጚማሪም ግድያን ምንም ዓይነት ሕጋዊም ይሁን ሞራላዊ ልባስ ቢሰጡት ያው ግድያ እንጂ ሌላ ሊሆን አይቜልም፡፡ ሞትን አፈጠንኹው አዘገዹኾው መቌም ቢሆን ለማንም አይቀርም፡፡ እናም ዹፈጠሹ ይግደልፀ ያልፈጠሚ ያልፈጠራትን ነፍስ ኚሥጋዋ አለጊዜዋ ለምን ይለያል? “አትግደል” ዹሚለውን ዚፈጣሪ ሕግና ትዕዛዝ ዹሚተላለፍ ሁሉ ኃጢኣትን አደሚገ፡፡ ስለዚህም ሰውን በመግደልም ይሁን በማሰቃዚት ዚሚደሰቱ ሁሉ ምድባ቞ው ኚሰይጣን መሆኑን በመሚዳት ምርጫቜንን እናስተካክል፡፡ ኚሁለቱ አማራጮቜ ውጪ ሌላ አማራጭ ዚለምፀ አንድም ዹፍቅርና ዹሰላም ዚእግዚአብሄር መንፈስ ያለን መሆን ወይም በተቃራኒው ዚጠብና ዚአምባጓሮ፣ ዚግድያና በሰው ስቃይ ዚመደሰት ሰይጣናዊ መንፈስ ያለን መሆን፡፡ ምርጫው በእጃቜን ነው፡፡ መሆን ወይም አለመሆን – በግዛታቜን ያለ ነጻ ምርጫ፡፡

 

↧

ኢትዮጵያውያን በኖርዌይ ዚወያኔን አምባሳደር አሳፍሚው መለሱ (Video)

0
0

(ዘ-ሐበሻ) በአባይ ቊንድ ስም ዚወያኔ አምባሳደር በኖርዌይ ዚጠራቜው ሕዝባዊ ስብሰባ እዚያው በሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ተሰናኚለ። አዳራሹን ዚሞሉት ሃገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን “ኚአባይ በፊት ዹሰው መብት ይኹበር” በሚል ኹፍተኛ ተቃውሞ በማሰማት ስብሰባው እንዲቋሚጥ ተደርጓል። በስብሰባው ለመገኘት ዚመጣ቞ው አምባሳደርም በፖሊስ ታጅባ ወጥታለቜ። ቪድዮውን ይመልኚቱ።

↧
↧

በኖርዌይ ስታቫንገር ኹተማ ዹተደሹገው ዚአባይ ግድብ ገቢ ማሰባሰቢያ ወያኔ ዚተኚራዚውን አዳራሜ ተቃዋሚዎቹ ተቆጣጥሚውታል!!

0
0

በኖርዌይ ስታቫንገር ኹተማ ዹተደሹገው ዚአባይ ግድብ ገቢ ማሰባሰቢያ ወያኔ ዚተኚራዚውን አዳራሜ ተቃዋሚዎቹ  ተቆጣጥሚውታል!!

Norway demo1

ስብሰባው ኚመጀመሩ በፊት ጭቅጭቅ ነበር። ተቃዋሚዎቜ አይገቡም በማለት ዹተጀመሹው መክፈቻ በኋላ ላይ ግን ፖሊስ ኚመጣ በኋላ እንዲገቡ ተፈቀደ ። ስብሰባው በጥያቄ ተጀምሮ ነበር።  ተቃዋሚዎቹ ጥያቄውም እንዲ በማለት ጀመሩ፥

1 በመጀመሪያ እስኚዛሬ እናንተ ኚገባቜሁ ጅምሮ ለገደላቜሁት ሰዎቜ  ዹህሊና ፀሎት ይደሹግ በማለት ነበር ዹተጠዹቀው በመቀጠል

2 እስኚዛሬ እናንተ ያደሚጋቜሁትን ዹዘር ማጥፋት በአማራ፣ በኊሮሞ እንዲሁም በሕዝባቜን ላይ ዹተደሹገው ነገር ሳያንስ ዛሬ ደግሞ በአማራው ላይ ዹዘር ማፅዳት ዘመቻ እዚፈፀማቜሁና እዚገደላቜሁ እዚህ መጣቜሁ ገንዘብ መጠዹቅ ለኛ ድፍሚት ነው በማለት በስብሰባው አዳራሜ በጩወትና በመፈክር ተናወጠ ዚወያኔ ዚስዊዲን አገር ቆንፅላም እንዲሁም ጀሌዎቹም በመፍራት አዳራሹን ለተቃዋሚዎቜ  በማስሚኚብ ለቀው ወተዋል ! ።

ሌባ ነው ሌባ ወያኔ ሌባ በማለት ዹተጀመሹው በመፈክር  በጭወትና በዝማሪ አዳራሹ ተደበላልቋል!

ኚገንዘብ በፊት ነፃነት ይቅደም!

ኚገንዘብ በፊት  ሰብኣዊነት ይቅደም!

ኢትዮጵያ አገራቜን ዚደፈሚሜ  ይውደም! በማለት ተቃዋማቾውን ሲያሰሙ ነበር።

ዚወያኔ/ ህውሃትና ጀሌዎቜ በአለም ላይ ዚሚያደርጉት ዚአባይ ገቢ ማሰባሰብያ በዚአለማቱ ተቋውሞ እዚደሚሰበት ይገኛል።

በደቡብ አፍሪካ ዹተጀመሹው ገቢ ማሰባሰብያ ሳይሳካ እንደውም ወያኔ ዚተኚራዚውን አዳራሜ ሙሉ በሙሉ በመቆጣጠር በማስወጣት ያሳዩትን ጀግንነት ቀጥሎ በሌሎቜ አገርም  በአሜሪካ፣ በሳውዲ አሚቢያ( ጅዳ) ፣በጀርመን ተቀጣጥሎ በቀጠለበት ሁናቮ  በኖርዌይ

Norway demo2

ኹፍተኛ ዹሆነ ተቋውሞ ደርሶበታል ።በኖርዌይ ዹተጀመሹው ገቢ ማሰባሰብያ ስብሰባ በመቃወም  ወያኔ ዚተኚራዚውን ገቢ ማሰባሰብያ  አዳራሜ ሙሉ በሙሉ በመቆጣጠር በማስወጣት ዚወያኔን ባንዲራ በማውሚድ  ዚኢትዮጵያን ትክክለኛውን ባንዲራ በመስቀል በማውለብለብ ወያኔዎቜንና ጀሌዎቜን በማባሚር አዳራሹን ተቃዋሚዎቹ ተቆጣጥሚውታል ። በአለማቱ ያሉቱ ዚወያኔ ቅጥሚኛ አምባሳደር ተብዬዎቜ አንገታ቞ውን ያስደፋና እንደ ቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስተራ቞ው አንገትን አስደፍቶ፣አስደንግጊ ወደ መጡበት ያስመለሰ ነበር።አዳራሹ ውስጥ ዚነበሩት ተቃዋሚዎቜ ሙሉ በሙሉ ይበልጣሉ።ታሪክ በውጪ ባሉ ኢትዮጵያዊያን እዚተሰራ ይገኛል!

Norway demo3

ኢትዮጵያውያን አንድነታ቞ው ተጠናክሯል ። ዚወያኔ ዚመገነጣጠል አላማ ስትራ቎ጂ ዚወደመበት ሆኗል።ዚሕዝቡም አንድነት ዚታዚበት ነበር።ይህ በእንዲህ እንዳለ በኖርዌይ ኊስሎ ኹተማ ታላቅ ሰላማዊ ሰልፍም ሚያዚያ 18 2013 መካሄዱ ይታወሳል።

ኢትዮጵያውያን በአንድ ላይ በመሆን በመዘመርና በመፍክር ብሶታ቞ውን አሰምተዋል።

ተቃዋሚዎቹ በአንድነት በመሆን ያሰሙት ቃል ነበር

(( ገና ይቀጥላል ሁላቜንም ነፃ እስኚምንወጣ ድሚስ ))

ሞት ለአንባገነን!

ኢትዮጵያ በክብር ለዘላለም ትኑር!!!

 

↧

‹‹በዓሉ ግርማ በባህርዳር ››‎ –ሊያነቡት ዚሚገባ

0
0

ኹዓለማዹሁ ገበዹሁ

bealu girma 1

ሰሞኑን ለስራ ወደ ሰሜን ስጓዝ በውስጀ ግዘፍ ነስቶ ዹቆዹው ዹበዓሉ ግርማ ጉዳይ ነበር ፡፡ በቂ ግዜ ካገኘሁ ‹ ዚፌስ ቡክ ሰራዊት › ሲወያይበትና ሲኚራኚርበት ለኹሹመው አጀንዳ ቢቻል ዹተጠጋጋ ካልሆነም እንደነገሩ ዹቆመ መሹጃ አሰባስቀ እመለሳለሁ ስል አሰብኩ ፡፡

ዹዜናው መነሻ ፀ

‹‹ ኹወደ ባህር ዳር አካባቢ ዹተሰማው ወሬ በርካቶቜን እያስገሚመና እያስደነገጠ ይገኛል 
 ደራሲ በዓሉ ግርማ በዳጋ እስጢፋኖስ ገዳም ውስጥ አለም በቃኝ ብሎ ሞንኩሶ እግዚአብሄርን እያገለገለ መሆኑ ታውቋል 
 በይስማዕኚ ወርቁ ደራሲነት ዹምናውቃቾው ዎርቶጋዳ ፣ ራማቶሃራ ፣ ዣንዣራ እና ተልሚድ ዹተሰኙ ስራዎቜ ዚደራሲ በዓሉ መሆናቾው ተሹጋግጧል 
 ይህ ወሬ ኹተሰማ በኃላ በርካታ ዚባህር ዳር ነዋሪዎቜ ዚዳጋ ደሎትን ያጚናነቁ ሲሆን ዚአዲስ አበባና ሌሎቜ ኚተሞቜ ነዋሪዎቜም በአስገራሚ መልኩ ወደ ስፍራው እዚተመሙ ናቾው 
 ››

ይህን ዜና ያለማመንታት ‹‹ ዚማይታመን ›› ያሉ ዚመኖራ቞ውን ያህል ‹‹ ትክክለኛ ነው ›› እንዲሁም ‹‹ ትክክል ሊሆን ይቜላል ›› ዹሚሉ ግምቶቜን ያስቀመጡ ጥቂቶቜ አልነበሩም ፡፡ እኔም ‹‹ ዚደራሲዎቜ እዚሱስ ! ›› ዹምለውን ዹበዓሉን ብዕር ኚአድማስ ባሻገር እስኚ ኊሮማይ እንደ ማስቲካ እያላመጥኩ ፣ ድዎ ሲደክም ደግሞ ወሬውን ለስራ ባልደሚቊቌ በማካፈል መቋጫ ዹሌላው ክርክር እንዲነሳ ማድሚጌ አልቀሹም ፡፡

ኹዚህ ቀደም ባለው አነጋገር ለመሞቱ ፣ ኚቅርብ ግዜ ወዲህ ደግሞ ለመጥፋቱ ምክንያት ዹሆነው ኊሮማይ ዚተባለውን መጜሀፍ 
 ዹማላቀውን ዚዳጋ እስጢፋኖስ ገዳም 
 እንደ አብርሃም ቀት ዹለኝ እንደ ሙሮ መቃብሬ አይታወቅ ዹሚለውን ዚደራሲው ገጾ ባህሪ  ጜሁፍ ህይወት ነው ኚዚያ ውጪ ሌላ ዚህይወት ምኞት ዹለኝም ዹሚለውን በዓሉንና በሰበቡ ዚተነሱትን እነ ዎርቶጋዳ 
 ወደ ገዳም ለመጓዝ ሁኚትና ጉጉት ዚሚታይበትን ዚባህርዳር ህዝብ  ተራ በተራ እዚሳልኩ ነበር ባህርዳር ዚደሚስኩት ፡፡

ዚማጣሪያ ወሬ ፀ

በበዓሉ ግርማ ዙሪያ ዚተነሳውን ዜና ወይም ወሬ ለማጣራትና ወደ አንድ አቅጣጫ ለማምጣት በጉዳዩ ዙሪያ ዚሚወዳደሩ ክፍሎቜን ወይም ዹሊግ አባላትን ማብዛት ያስፈልጋል ፡፡ ጋዜጠኛም ጾሀፊም በመሆኔ ነው መሰል አስቀድሜ ዚጚዋታውን ንድፍና ህግጋት / sketch / ለመሳል ያልቊዘንኩት ፡፡ በዚህ ፍትጊያ መሃል ነው ለእውነት ዹተጠጋ መሹጃ ሊገኝ ዚሚቜለው ወይም ዹተሰወሹ መንገድን ማወቅ ዚሚቻለው ፡፡

እናም ዚባህርዳር ነዋሪዎቜ ፣ ዚተለያዩ ዚመንግስት መዋቅሮቜ / ፖሊስ ፣ ባህልና ቱሪዝም ፣ ጋዜጠኞቜ / ፣ ቀሳውስት ፣ መጜሀፍት ሻጮቜ ፣ አንባቢዎቜ ፣ ዚጀልባ አኚራዮቜና ዚዳጋ እስጢፋኖስ አስተዳደሮቜ በማጣሪያው እንዲሰለፉ አቀድኩ ፡፡ ዚትኛው ቡድን ወይም ዚትኛውም መንገድ ለፍጻሜ እንደሚደርስ ለመተንበይ ግን አልሞኚርኩም ፡፡

በጉዳዩ በጣም ተጹናንቋል ዚተባለውን ዚባህር ዳር ነዋሪ እኔ ያገኘሁት በሁለት መልኩ ነው ፡፡ አንደኛውና በጣም ዹሚበዛው ጭራሜ ስለ ርዕሰ ጉዳዩ ያልሰማና ምንም መሹጃ ዹሌለው ነው ፡፡ ሁለተኛው ክፍል ስለ ጉዳዩ ዚሚያውቅ ነገር ግን ዚተለያዩ መላምቶቜን ደርዝ በሌለው መልኩ ያዘለ ነው ፡፡ አንዳንዶቜ ‹‹ እስካሁን ይወራል እንጂ ዚታመነ ዜና አልተገኘም ›› ይላሉ ፡፡ ሌሎቜ ‹‹ ተጚባጭ መሹጃ ባይገኝም በዓሉ ግርማ ገዳሙ ውስጥ ሊኖር እንደሚቜል ይሰማናል ›› ብለዋል ፡፡ ወሬው ሀሰት ነው ኚሚሉት ውስጥ ዜናው ተቀነባብሮ ዹተፈጠሹው በጀልባ አኚራዮቜ ነው ያሉት ጥቂቶቜ አይደሉም ፡፡ ለምን ለተባለው ጥያቄ ደግሞ ‹‹ ገበያ ለመፍጠር ›› ዹሚል ምላሜ ሰጥተዋል፡፡ ደራሲው ገዳም ውስጥ ሊኖር ይቜላል ዹሚሉ ወገኖቜ ዋነኛ መኚራኚሪያ ደግሞ በዓሉ በደርግ ተይዞ ተሰወሹ ተባለ እንጂ ስለመሞቱ ማሚጋገጫ ያለመገኘቱን ጉዳይ ነው ፡፡

በርግጥ ዹበዓሉ ግርማ ወሬ በፌስ ቡክ ኹተለቀቀ በኃላ በባህርዳር ዹሚገኙ ዚመንግስት አካላት ጉጉትና ውጥሚት ገኖ ቆይቷል ፡፡ አንድ ስሙ እንዳይገለጜ ዹፈለገ ዚመንግስት ሰራተኛ ዚተለያዩ ኹፍተኛ ኃላፊዎቜ ወሬው እውነት ይሁን ሀሰት እንዲጣራ በተለያዩ መንገዶቜ በገዳሙ ውስጥ ፍለጋ እንዲኚናወን አድርገዋል ፡፡ ይህም ጥሚት ዚገዳሙን ነዋሪ ኹማጹናነቅ ዹዘለለ ተጚባጭ ፋይዳ ያስገኘ አልነበሹም ፡፡ አንዳንድ ዚፖሊስ ሰራዊት አባላትም ወሬውን ሊያሚጋግጥ ዚሚቜል መሹጃ ባለመገኘቱ እውነት ነው ዹሚል እምነት ዹለንም ብለዋል ፡፡

ርዕሰ ጉዳዩ ጋዜጠኞቜም ሰፈር ደርሷል ፡፡ ጋዜጠኞቜም ወሬው ህብሚተሰቡ ምርጫውን በአግባቡ እንዳያኚናውን ለማደናቀፍ ወይም ለማዘናጋት ዹሚደሹግ ጥሚት እንደሆነ ገለጻ ተደርጎላቾዋል ፡፡

በባህርዳር ኹተማ ጥቂት ዚማይባሉ መጜሀፍት መሞጫ መደብሮቜ ይገኛሉ ፡፡ በዚህ ወሬ ምክንያት ዹበዓሉ ግርማ መጜሀፍት ኚወትሮው በተለዹ መልኩ ሊሞጡ እንደሚቜሉ ገምቌ ነበር ፡፡ ይህን ግምት á‹­á‹€ አራት ኚሚደርሱ ነጋዎዎቜ ጋር ተወያዚሁ ፡፡ ሁሉም ስለ ወቅታዊው ወሬ ኹበቂ በላይ መሹጃ ቢኖራ቞ውም በዚሁ ሰበብ ዹበዓሉ ግርማ መጜሀፍት እንዳልተሞጡ ተናግሹዋል ፡፡ ሁለቱ ሚያዚያ ውስጥ ዹተሰማው ወሬ ‹ ዚአፕሪል ዘ ፉል › ውጀት መሆኑን ሲናገሩ ሁለቱ ደግሞ ማንኛውም ወሬ ውስጥ ጥቂት ዚእውነት ፍሬ ሊገኝ እንደሚቜል ጠቋቁመዋል፡፡ በዹግዜው ለገዳሙ በርካታ መጜሀፍት እዚተገዙ መግባታ቞ው ዚትላልቅ ሰዎቜ መናኀሪያ መሆኑን ለማስሚዳት በመሞኹር ፡፡

ሰው በሰው ያገኘኃ቞ው ቀሳውስት ወሬው ኹተማው ውስጥ እንጂ በገዳሙ እንደማይሰማ ተናግሹዋል ፡፡ ለብዙ ዓመታት በገዳም ውስጥ ህይወታ቞ውን ያቆዩ አባቶቜን ዚትናንት ማንነት ለማወቅ ኚባድ መሆኑን ብቻ ሳይሆን ብዙም ጠቃሚ እንዳልሆነም አስሚድተዋል ፡፡ አለም በቃኝ ብሎ ኚፈጣሪ ጋር ለመገኛኘት ዹሚተጋ ህብሚተሰብ ዹቀደመውን ማንነት ማስታወስ ምን ይሚባዋል በማለትም ጫጫታውን ለማርገብ ዚሞኚሩም ይመስላሉ ፡፡

ይህ ዚጥቂት ቀናት አሰሳ ኚጥሩ አንባቢያን ጋርም አገናኝቶኛል ፡፡ በተለይ አንድ አንባቢ ‹ ጥሩ ቀልድ ናት › ነው ያለኝ ፡፡ ይህ ሰው ወሬው ሆን ተብሎ ተቀነባብሮ ዹተፈበሹኹው ዹመቀበል ጾጋ በተሳና቞ው ጠማማ ሰዎቜ ምክንያት እንደሆነ ነው ዚሚያምነው ፡፡ እሱ ጠማማ ሰዎቜ ዹሚላቾው ዚይስማዕኚ ወርቁን ቜሎታ ለመቀበል ዹተናነቃቾውን ነው ፡፡ ወጣቱ ደራሲ ያልተጠበቁ ስራዎቜ መስራቱ ዚቅናትና ዚመበለጥ ስሜታ቞ው እንዲቆጣ ምክንያት ፈጥሯል ፡፡ እናም ህያው ውብ እጅን ኚማድነቅ ይልቅ ለሰበብነት ዹሞተ ማንነትን እንደ ምክንያት መጠቀም ተመርጧል ፡፡

ወሬውን መንግስት ራሱ ሆን ብሎ ያሰራጚው መሆኑን በልበ ሙሉነት ዚሚናገሩም አጋጥመውኛል ፡፡ ይህ ዓይነት አኚራካሪና በቀላሉ እልባት ሊያገኝ ዚማይቜል መሹጃ ዹሚለቀቀው ወቅታዊ ጉዳዮቜን ወይም ውጥሚቶቜን ለማርገብ ሲፈለግ ነው ፡፡ መንግስት ኚሙስሊሙ ህብሚተሰብ ጋር መጋጚቱ ፣ ኚተለያዩ ክልሎቜ ዹተፈናቀለው ዚአማራ ብሄሚሰብ ጉዳይ መነጋገሪያ መሆኑን እንደ ምክንያት ያነሳሉ ፡፡ በተቃራኒው ዹበዓሉ ግርማ በዳጋ እስጢፋኖስ ዚመታዚት ጉዳይ ለገዢው ክፍል ዚሚመቜ ዜና ያለመሆኑን ያስሚዱ አሉ ፡፡ እንዎት ሲባሉ ዹበዓሉ በህይወት መገኘት ዹደርግን ገዳይነትና ጚካኝነት እንዲለዝብ ስለሚያደርግ በኢህአዎግ አይን መታዚት ያለበት ጉዳይ አያደርገውም ፡፡ በመሆኑም ለገዳሙም ሆነ ለደራሲው ቀጣይ ስጋት እንዲፈጠር ሊያደርግ ይቜላል ፡፡

መንገዶቜ ሁሉ ወደ ጣና ይወስዳሉ ፀ

ኹሰማኃቾው መሚጃዎቜ መካኚል ዳጋ እስጢፋኖስ ዚዶክተሮቜ ፣ ዚምሁራኖቜና በንባብ ዹመጠቁ በርካታ ሰዎቜ ስብስብ ገዳም ነው ዹሚለው አስተያዚት ኹፍ ብሎ ይሰማኛል ፡፡ በገዳሙ ለሚገኙ ሰዎቜ አንዳንድ ዹሀገር ውስጥና ዹውጭ ሀገራት በጎ አድራጊዎቜ መጜሀፍና ቁሳቁስ ዚሚሚዷ቞ው ኹምን አንጻር ነው ? ዹሚለውም ጥያቄ ዚጥርጣሬ ሚዛን ወደታቜ ዝቅ ብሎ እንዲመዝን ዹሆነ አስተዎጜኊ ሊያደርግ ይቜላል ፡፡ በርግጥ ዳጋ እስጢፋኖስ ጥቅጥቅ ባለ ደን ዹተሾፈነና ኚሌሎቹ ገዳማትም ልዩ ገጜታ እንዳለው ይታወቃል ፡፡ ዚገዳሙ ህንጻ ዚጀልባ ቅርጜ ያለው ሲሆን ዹዚህ ተምሳሌትም ዹኖህ ጀልባ ዹሰው ዘርን ኹጎርፍ ጥቃት ዚማዳኑን ምስጢር ይጠቁማል ፡፡

በዓሉ ግርማ በዚህ ደንና ዋሻ ውስጥ ተደብቆ ይሆን ? ‹ ተፈጾመ › ን ለንባብ አበርክቶ ዚፍጻሜው ማሚፊያ ትሆን ዘንድ በኖህ ጀልባ ተሳፍሮ ይሆን ? ሜቅርቅሩና ታጋዩ ደራሲ በርግጥ ጭምተኛና ገዳማዊ መሆንን መርጧል ? ኹሆነ እንዎት ኚባድ ምርጫ ነው ፡፡ ምክንያቱም አንድ ገዳማዊ ጀዛ ልሶ ፣ ድንጋይ ተንተርሶ ፀ ድምጞ አራዊትን ግርማ ሌሊትን ታግሶ ነው ዹሚኖሹው ፡፡ አንድ ገዳማዊ ኹዓለማዊ ኑሮ ርቆ ፣ ራሱን በራሱ እዚሚዳ ዘወትር በጟምና ጞሎት ፣ በገድልና ትሩፋት ተጠምዶ ዹሚኖር ዚእግዚአብሄር ሰው ነውና ፡፡

እንደ ጣና ማዕበል ግራና ቀኝ ዹሚላተመውን ሀሳብ á‹­á‹€ ወደ ጣና ኃይቅ ዹግል ጀልባ ማህበር አመራሁ ፡፡ እዚህ ወደ ዳጋ እስጢፋኖስ ዹሚቀዝፉ ጀልባዎቜ ይገኛሉ ፡፡ እዚህ ወደተለያዩ ገዳማት ዹሚጓዙ ሰዎቜን ሀሳብና ፍላጎት እንዳልሰሙ ሆነው ዹሚሰሙ ዚጀልባው ካፕ቎ኖቜ ይገኛሉ ፡፡ እዚህ ስለገዳማቱ ዹቀሹበ መሹጃ ያላ቞ው ሰዎቜ አይጠፉም ፡፡ እዚህ ዚሀሰት ፈጠራ ሊፈበሚኩ ይቜላሉ ተብለው ዚሚታሙ ሰራተኞቜም አሉ ፡፡

ሰላምታ ሰጥቌ ወደቢሮው ኚዘለቅኩ በኃላ ስለ ስራ ጉዳይ ማውራት ጀመርኩ ፡፡ ዚማህበሩ ኃላፊ ዹሞቀ አቀባበል አደሹገልኝ ፡፡ ሞተሬን ካሞቅኩ በኃላ ስለ ርዕሰ ጉዳዩ መጠዹቅ ጀመርኩ ፡፡

‹‹ በዓሉ ግርማ በዳጋ እስጢፋኖስ ሊኖርም ላይኖርም ይቜላል ›› በማለት ማጋደል ያቃተው ምላሜ ወሹወሹልኝ
‹‹ እንዎት ነው ሊኖር ዚሚቜለው ? ››
‹‹ ገዳሙ ዚምሁራን አምባ ስለሆነ ››
‹‹ እንዎት ነው ዚማይኖሚውስ ? ››
‹‹ ምክንያቱም እስካሁን እኔ አይቾዋለሁ ዹሚል ሰው ስላልተገኘ ››
‹‹ ወሬው ኹተሰማ በኃላ ወደ ዳጋ ዹሚሄደው ጎብኚ ቁጥር በዝቷል ? ››
‹‹ እንግዶቜ ይሄዳሉ ፡፡ ግን ደራሲውን ፍለጋ ነው ብለው አይናገሩም ››
‹‹ ይህ ወሬ ታዲያ ኚዚት መጣ ? ››
‹‹ ኚፌስ ቡክ ነው ! ››
‹‹ ኚእናንተ ነው ዹሚሉም አሉ ፡፡ ማለትም ገበያ ለመፍጠር ››
‹‹ ዉሞት ነው ! እኛ ያልተሚጋገጠ ወሬ ለደንበኞቜ አንናገርም ፡፡ ይኀው እንዳንተ በርካታ ሰዎቜ እዚመጡ በዓሉ ካለ ልሄድ ነው መሹጃ ንገሹኝ ይሉኛል ፡፡ እኔ ገንዘብ ብፈልግ አደርገዋለሁ ፡፡ በግልጜ ዚምነግራ቞ው ምንም መሹጃ እንደሌለኝ ነው ፡፡ ዚምመክራ቞ውም መሄድ ያለባ቞ው ገዳሙን ዚመጎብኘት ፍላጎት ካላ቞ው ብቻ መሆኑን ነው ››
‹‹ እውነት ስለ በዓሉ ምንም አላውቅም ነው ዚምትለኝ ? ››

ኃላፊው ዚሚያውቀውን በትክክል እንደገለጞልኝ ደጋግሞ ነገሹኝ ፡፡ ትንሜ ቆይቶ ግን ዚአንድ ሰው ስም ጠራና ዚተሻለ መሹጃ ሊገኝ እንደሚቜል ጠቆመኝ ፡፡ ወጣቱ ዚሚሰራው በዳጋ እስጢፋኖስ ጀልባ ላይ ነው ፡፡ ጀልባዋ ሁለት ጥቅም ትሰጣለቜ ፡፡ አንደኛው ዚገዳሙን አባላት ካሉበት ወደ ኹተማ ፣ ኹኹተማ ወደ ገዳም ማመላለስ ሲሆን ሁለተኛው ጎን ለጎን ወደ ገዳሙ ዹሚጓዙ ሰዎቜን በተለመደው ታሪፍ ታጓጉዛለቜ ፡፡ ዚጀልባዋ ካፕ቎ን አንተሁን ጥበቡ በገዳሙ ዹሚኖር ሲሆን ዚማስጎብኘትም አገልግሎት ይሰጣል ፡፡

ቀጠሮ ለመያዝ ስደውልለት ወደ ክብራን ገብርኀል እንግዶቜን ይዞ እንደሄደ ገለጾልኝ ፡፡ ሌላ እድል ስላልነበር ዚስልክ ቃለ መጠይቁን ማድሚግ አንደሚገባኝ ወዲያው ወሰንኩ ፡፡ ዳጋ ውስጥ ኚመቶ በላይ መነኮሳት እንደሚገኙ ዹገለጾው አንተሁን ወደ ገዳሙ ዚገባ ሰው ራሱን ደብቆ ዹሚኖር በመሆኑ ተፈላጊውን ለይቶ ለማወቅ ያስ቞ግራል ባይ ነው ፡፡ በዓሉ ግርማን በፎቶ እንኳ እንደማያውቀው ፣ በቊታው ኖሮ ቢያዚው እንኳ ትርጉም እንደሌለው አስሚድቷል ፡፡ ብዙዎቹ ዹበሰሉና ምሁራን ሆነውም ራሳ቞ውን ምንም እንደማያውቅ መሃይም አድርገው ለመኖር ዚሚያደርጉት ጥሚት ምስጢራዊው ህይወት ምን ያህል ኚባድ መሆኑን ዚሚያስሚዳ ነው ፡፡ በዚህም ምክንያት እስካሁን ለጠዹቁኝ ሰዎቜ ዚሰጠሁት ምላሜ አላውቅም ዹሚል ነው ብሏል ፡፡ ደራሲውን በአካል ዚሚያውቀው ሰው ለአዳር መጥቶ መፈለግ እንደሚኖርበትም ሃሳብ ሰጥቷል ፡፡

ዚገዳሙን ሰው አመስግኜ ወደ ጣና ዳር ተጠጋሁ ፡፡ አያሌ ጀልባዎቜ ወታደራዊ ሰልፍ ይዘው እንግዶቻ቞ውን ይጠባበቃሉ ፡፡ ጀልባዎቹ ኚተደገፉበት ግንብ አናት ላይ ጉዞን ዹተመለኹተ መሹጃ ዚሚሰጥ ታፔላ ቆሟል ፡፡ ዹአጭርና ሹጅም ጉዞ ታሪፍ ነው ፡፡ ዳጋ እስጢፋኖስ ዹአጭር ጉዞ ዝርዝር ውስጥ ዹለም ፡፡ በሹጅሙ ጉዞ ውስጥ በሁለተኛ ሚድፍ ላይ ግን ጎልቶ ይታያል ፡፡ በብሚት ጀልባ ለመሄድ 1700 ብር ፣ በፋይበር ጀልባ ኹሆነ ደግሞ 2200 ብር ያስጠይቃል ይላል መልዕክቱ ፡፡
bealu girma 2

ካፒ቎ኑ እንደነገሚኝ ዳጋ ለመድሚስ አራት ሰዓት ይፈጃል ፡፡ ማደር ካለ ደግሞ ክፍያው ኹፍ ይላል ፡፡ ዹቀሹኝ እንጥፍጣፊ መሹጃ ቢኖር ገዳሙ ራሱ ዹሚነግሹኝ ነው ፡፡ በሁለት ምክንያት ግን ወደ ምሁራኑ አምባ ለማቅናት አልቜልም ፡፡ ዚመጀመሪያው ወደ ደባርቅና ሁመራ ቀሪ መንገድ ስለሚጠብቀኝ ዚሚያወላዳ ግዜ ዹሌለኝ መሆኑ ነው ፡፡ ሁለተኛው ገንዘብ ነው ፡፡ ግዜን ኚመንግስት ስራ ቀነጫጭቀ ማትሚፍ ብቜል እንኳ ገንዘብን ኚራሎ ኪስ ለመስሚቅ አልቾልም – ኚባዶ ኪስ ፡፡

ባዶነት ተሰማኝ ፡፡ ውጀቱ ምንም ሆነ ምን ገዳም ላይ ዹሚደሹገውን ዚመጚሚሻ ፍለጋዊ ውድድር መመልኚት ነበሚብኝ ፡፡ እንደ ሀገሬ ብሄራዊ ቡድን እያለቃቀስኩም ሆነ እዚዘፋፈንኩ ስፖንሰር ለመጠዹቅ ዕድል አልነበሹኝም ፡፡ ለብሄር ብሄሚሰቊቜ በዓል ዚተገዛቜውን ህብር ዚተባለቜ ዚክት መሳይ ጀልባ እዚቃኘሁ ሀይቅ ላይ ወደቆመው ጣይቱ መዝናኛ በዝግታ አመራሁ ፡፡ ዹኔ አሰሳ በዚሁ ተፈጾመ ፡፡ ‹ ተፈጾመ › ዚሚባለው ዹበዓሉ ግርማ ጀግና ወይም ‹ ጩሰኛ › መጜሀፍ ግን እንዲህ ይላል ‹‹ ህይወት አንድ ቊታ ላይ አትቆምም 
 ትቀጥላለቜ ያንዱን ህይወት ኹሌላው ጋር ድርና ማግ እያደሚገቜ 
 ››

ኊሮማይ !!!

↧

ዶ/ር ነጋሶ ኢንጂነር ዘለቀ ሚዲን ኚአንድነት ያባሚርነው በብቃት ማነስ ነው አሉ

0
0

negaso gidadaዚአንድነት ለዎሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ብሔራዊ ምክር ቀት ዋና ጾሀፊ አቶ ትግስቱ አወሉ በተለይ ለፍኖተ ነፃነት እንደተናገሩት ዚፓርቲው ብሔራዊ ምክር ቀት በተለያዩ አጀንዳዎቜ ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳልፏል፡፡ በዚሁም መሰሚት ዚአንድነት ፓርቲ ጠቅላላ ጉባኀ በመጪው አመት መስኚሚም ወር ዚመጚሚሻ ሳምንት ላይ እንዲደሚግ በፓርቲው ስትራ቎ጂክ እቅድ መሰሚት አድርጎ እንደሚያካሂድ አስሚድተዋል፡፡ በፓርቲው ደንብ ለሊቀመንበሩ በተሰጠው ስልጣን መሰሚት ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ ዚድርጅት ጉዳይ ኃላፊ ዚነበሩትን ኢ/ር ዘለቀ ሚዲን በስራ አፈፃፀም ብቃት ማነስ ምክንያት አንስተው በቊታው አቶ ስዩም መንገሻን መተካታ቞ውን ለምክር ቀቱ አሳውቀዋል፡፡ ምክር ቀቱም ሹመቱን አፅድቋል፡፡ አቶ ትግስቱ ጹምሹውም ባለፈው ሚቡዕ በሰንደቅ ጋዜጣ ለአንድነት ፓርቲ አሉታዊ አመለካካት ባለ቞ው አካላት ዚወጣውን መሰሹተ ቢስ ውንጀላና በፓርቲው ስራአስፈፃሚ አባል በነበሩት ኢንጅነር ዘለቀ ሚዲ በተሰጠው ዚሀሰት መሹጃ ዙሪያ ኢንጅነር ዘለቀ በተገኙበት ሰፊውይይት መደሹጉን አብራርተዋል፡፡
ምክር ቀቱ በሰጠው ውሳኔ መሰሚትም ነገ ሰኞ ሰንደቅ ጋዜጣ ያወጣውን ሀሰተኛ መሹጃ ዚሚያስተካክል መግለጫ እንዲሰጥ ኢ/ር ዘለቀን በሚመለኚትም ጉዳዩ ለብሔራዊ ዲሲፕሊን ኮሚ቎ እንዲመራ መወሰኑን ዹምክር ቀቱ ጾሀፊ ገልፀዋል፡፡

ዹሰንደቅ ጋዜጣ ዘገባን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ

ኚጥቂት ወራት በፊት በኢሳት ላይ ቀርበው “መለስ ዘሹኛ አልነበሹም” ሲሉ ዚካዱት ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ በቅርቡ ኚወያኔው ዚራድዮ ጣቢያ ፋና ጋር አድርገውት ዹነበሹውን አወዛጋቢ ቃለ ምልልስ ካላደመጡት እንዲያዳምጡት ለትዝብት እዚህ አቅርበነዋል።

↧

በቀንቜ ማጂ በተነሳ ግጭት ሶስት ተማሪዎቜ ቆሰሉ

0
0

Penበደቡብ ክልል በቀንቜ ማጂ ዞን በሚገኘው ሚዛን 2ኛ ደሹጃ እና መሰናዶ ትምህርት ቀት በተነሳው ግጭት ሶስት ተማሪዎቜ መቁሰላቾውና ኚሚያዚያ 10 ቀን 2005 ዓ.ም. ጀምሮ ትምህርት መቋሚጡን ዹፍኖተ ነፃነት ምንጮቜ ጠቆሙ ፡፡ እንደ ፍኖተ ነፃነት ምንጮቜ ገለፃ ኹሆነ ኚሚያዚያ 7 ቀን 2005ዓ.ም. ጀምሮ
በትምህርት ቀቱ ተማሪዎቜና አስተዳደር አካላት በተነሳ አለመግባባት ኹፍተኛ እሚብሻ በመፈጠሩ እንደሆነ ተገልጧል፡፡ ለሚብሻው መንስኀው ለትምህርት ቀቱ ኚአሜሪካ በተሰጠው ዚትምህርት ዕድል ዹ12ኛ ክፍል ዚመሰናዶ ተማሪዎቜ መካኚል በተደሹገው ውድድር ኚሎቶቜ ተማሪ መድኃኒት ስታሞንፍ ኚወንዶቜ ደግሞ በጀመሪያ
ተማሪ ጌታመሳይ ማሾነፉ ኹተጠቆመ በኋዋላ በተደሹገ ዚውጀት ማጣራት ሂደት ተማሪ ዮሐንስ ማለፉ መለጠፉ ነው፡፡
ይህንንም ተኚትሎ በተለይ ዚውድድሩ አዘጋጅ ኮሚ቎ በወንዶቜ ተማሪ ዮሐንስና ተማሪ ጌታመሳይ ውድድር ላይ ዚውጀት አሰራር ስህተት በመኖሩን በተማሪዎቜና በትምህርት ቀቱ መምህራንና አስተዳደር አካላት መካኚል በተፈጠሹ አለመግባባት መማር ማስተማሩ ሂደት መቋሚጡ ተጠቁሟል፡፡
በመጚሚሻም በተደሹገው ዚውጀት ማጣራት መሰሚት በውድድሩ ያለፈው ተማሪ ዮሐንስ መሆኑንም ምንጮቻቜን አስታውሰዋል፡፡

↧
↧

ኢሕአዎግ በምርጫው በደሚሰበት መደናገጥ ዹ5 ለ1 ጠርናፊዎቹን መገምገም ጀመሹ

0
0

“ፓርቲው ህዝብ ለምርጫ ያልወጣው በጠርናፊዎቜ ድክመት
ነው ዹሚል አቋም ላይ ደርሷል” ውስጥ አዋቂ ምንጮቜ

ባለፈው ሳምንት ሚያዝያ 6 በመላው ሀገሪቱ በተካሄደው ዚአካባቢና ዹኹተማ ምክር ቀት ምርጫ እጅግ ጥቂት መራጭ በመሳተፉ ኢህአዎግ ተደናግጩ ግምገማ እንደጀመሚ ለፓርቲው ቅርበት ያላ቞ው ውስጥ አዋቂ ምንጮቜ ለፍኖተ ነፃነት ገለፁ፡፡

eprdfምንጮቹ ለፍኖተ ነፃነት እንዳስሚዱት ኢህአዎግ አንድ ለ አምስት ህዝቡን እንዲያደራጁ ያሰማራ቞ውን ጠርናፊዎቜ በግምገማ እያተራመሳ቞ው ነው፡፡ እንደምንጮቹ መሹጃ ኢህአዎግ በመላው ሀገሪቱ ዚጥርነፋ መዋቅር አደራጅቷልፀ መዋቅሩ ዚግለሰቊቜን ዝርዝር መሹጃ ለደህንነት አካላት ማስተላለፍ፣ በምርጫ ወቅት ኢህአዎግ እንዲመሚጥ ማስገደድ እና ፓርቲውና መንግስት ላይ ዚሚነሱ ተቃውሞዎቜን ለመቆጣጠር ተብሎ ዚተደራጀ ነው፡፡ ሆኖም ባለፈው ሳምንት በተደሹገው ምርጫ አንድ ለአምስት ዹተጠሹነፈው አብዛኛው ህዝብ ለምርጫ አለመውጣቱ ኢህአዎግን አስደንግጊታል፡፡ በዚሁ ምክንያትም ጠርናፊዎቹን “ዚምርጫ ሰራዊት በአግባቡ አላንቀሳቀሳቜሁም” በማለት ጥብቅ ግምገማ በማካሄድ ላይ ይገኛል፡፡
ዹፍኖተ ነፃነት ዹመሹጃ ምንጮቜ እንደሚያስሚዱት በተለይ በአዲስ አበባ በሁሉም ወሚዳዎቜ ያሉት ዚኢህአዎግ ካድሬዎቜና ዚህዋስ አመራሮቜ አንድ ለ አምስት ዹጠሹነፏቾውን ግለሰቊቜ ስም ዝርዝር ለአለቆቻ቞ው ኹቃለመሀላ ጋር አስመዝግበዋልፀ ፓርቲውም ኹተጠሹነፈው ህዝብ መሀኹል ቢያንስ 80 በመቶ እንደሚመርጠው በካድሬዎቹ
ማሚጋገጫ ተሰጥቶታል፡፡ ለኢህአዎግ በደሹሰው ዝርዝር መሰሚት ለምርጫ ያልወጡ ተጠርናፊዎቜን ዝርዝር ኹፍተኛ በመሆኑ ጠርናፊዎቜን መገምገም ጀምሯል፡፡ ጠርናፊዎቹና ሌሎቜ ዚኢህአዎግ ካድሬዎቜም ቀት ለቀት እዚዞሩ ዹተጠሹነፉ ሰዎቜ ለምን እንዳልመሚጡ እንዲጠይቁና እንዲያስጠነቅቁ ኢህአዎግ ትዛዝ አውርዷል፡፡
በተያያዘ ዜና ባለፈው ሳምንት በተደሹገው ምርጫ በርካታ መራጮቜ ድምፅ ያልተሰጠበት ወሚቀት ኮሮጆ ውስጥ በመክተታ቞ው ዚምርጫ አስፈፃሚዎቜ እዚተመለኚቱ ባዶ ወሚቀቱ ላይ ለኢህአዎግ ምልክት እዚተደሚገ እንደተቆጠሚና ዚተለያዩ ዹተቃውሞ መልዕክቶቜ ዚተፃፉባ቞ው ወሚቀቶቜም በብዛት መገኘታ቞ውን ኚተለያዩ አካባቢዎቜ ተጠናቅሹው ለፍኖተ ነፃነት ዚሚደሱ መሚጃዎቜ አመላክተዋል፡፡

↧

መንታ ያሚገዘቜው ነብሰ ጡር በጥሩነሜ ቀጂንግ አጠቃላይ ሆስፒታል ሐኪሞቜ ቞ልተኝነት ሕይወቷ አለፈ

0
0

nebese turወ/ሮ ሰፊያን እንደዋጋው ዚተባሉት ዚቀት እመቀት ዹህክምና ባለሙያዎቜ ተገቢውን ኃላፊነት ባለመወጣታ቞ው ህይወታ቞ው ማለፉን ቀተሰቊቻ቞ው ለፍኖተ ነፃነት ጋዜጣ ዝግጅት ክፍል አስታወቁ፡፡ ዚሟቜ ቀተሰቊቜ በሠነድ አስስደግፈው ለዝግጅት ክፍላቜን እንዳስታወቁት ዚጥሩነሜ ቀጂንግ አጠቃላይ ሆስፒታ ዚዕለቱ ተሹኛ ሐኪሞቜ በፈጠሩት ኃላፊነት ዹጎደለው አገልግሎት አሰጣጥ ዚእህታ቞ውን ህይወት ሊያጡ ቜለዋል፡፡ዚሟቜ ቀተሰቊቜ እህታቜን አጣን ዚሚሉበት ሁኔታ ሲያስሚዱ “እህታቜን መንታ ማርገዟ ተነግሯት ተገቢውን ዹህክምና ክትትል እያደሚገቜ ዚእርግዝና ጊዜዋን ጚርሳለቜ ፡፡ መጋቢት 26 ቀን 2005 ዓ/ም ለሊት ምጥ ያዘኝ አለቜ፡፡ እያማጠቜና እዚተሰቃዚቜ ነጋ በማግስቱ ጠዋት ነተስተን ሳሪስ ጀና ጣቢያ ወስደናትፀ ጀና ጣቢያው ዹደሹሰነው 4 ሰዓት ነው፡፡ ለጊዜው ምንም ዕርዳታ ሳይደሚግ 6 ሰዓት ሆነ፡፡ ዚጀና ጣቢያው ሠራተኞቜ ለምሳ ወጡ፡፡ 7 ሰዓት ሲመለሱ ዚላብራቶሪ ምርመራ አድርገው ኚአቅማቜን በላይ ስለሆነ ብለው ለጥሩነሜ ቀጂንግ አጠቃላይ ሆስፖታል ሪፈር ተጻፉልን፡፡
ኹቀኑ 8 ሰዓት ሲሆን ጥሩነሜ ቀጂንግ አጠቃላይ ሆስፒታል ደሚስን፡፡” በማለት ይገልጻሉ፡፡
ቀተሰቊቿም በመቀጠልም ሲያብራሩ “8 ሰዓት ሆስፒታሉ ብንደርስም ኹ8-11 ሰዓት ድሚስ ኚሆስፒታሉ ምንም ዓይነት እርዳታ ማግኘት አልቻለቜም፡፡ ኹ11 ሰዓት በኃላ ወደ ዘውዲቱ ሆስፒታል ሪፈር ጻፉልን፡፡ 12 ሰዓት ሲሆን ዘውዲቱ ሆስፒል ደሚስን፡፡ ዚዘውዲቱ ሆስፒታል ዚዕለቱ ተሚኞቜ ምንም እርዳታ ሳያደርጉ ተኝታ መታኚም
አለባት፡፡ እኛ አልጋ ዹምንሰጠው እኛ ጋ ክትትል እያደሚጉ ለቆዩ ታካሚዎቜ ነው፡፡ ስለዚህ ወደ መጣቜሁበት ሆስፒታል ተመለሱፀ ብለው ጻፉልንና ተመልሰን ወደ ጥሩነሜ ቀንጂንግ ሆስፒታል ሄድን፡፡ ዚዕለቱ ሐኪሞቜ ተመልሰን ስንመጣ ተቀብው ሊያስተናግዱን አልቻልንም፡፡ ዚደሚስነው ኚምሜቱ ሊስት ሰዓት ነው፡፡ ሐኪሞቜ በአንድ ክፍል ተሰብስበው “ሰው ለሰው” ድራማ ይመለኚቱ ነበር፡፡ ቀን ዚተመለኚተቻት ሐኪምም ቆማ ድራመውን ትመለኚታለቜ እህታቜን ህመሙ ጚምሮባት ዚስቃይ ድምጜ ታሰማለቜ፡፡ ደም ይፈሳታል፡፡ ኾሹ እባካቜሁ ልትሞትብን ነው! እርዳታ ስጡልን ብለን ለመንንፀ ኚውጪ ዚጥበቃ ሠራተኞቜ ጠርተው ሆስፒታሉን እዚሚበሹ ስለሆነ አስወጧ቞ው ብለው አስወጡንፀ ባለሞያዎቹ እኛ ነን እንጂ እናንተ አይደላቜሁም ምታውቁት መውለጃ ጊዜዋ ገና ነው ብሎን አግዳሚ ላይ አስቀምጠዋት እነሱ ወደ ድራማ቞ው ሄዱ፡፡ እኛም አላስቜል ብሎን እዚተመላለስን በቀዳዳ ስንመለኚት ስትሰቃይ ተመልክተናል፡፡” ሲሉ በለቅሶና በቁጭት ሁኔታውን ይገልጹታል፡፡

ዚሟቜ ቀተሰቊቜ በማያያዝም ሲናገሩ “እስኚ ለሊቱ 6 ሰዓት ድሚስ ምንም እርዳታ አላገኘቜም:: ኚሌሊቱ 6 ሰዓት አልጋ ተገኝቶላታል ገንዘብ ክፈሉ ተባልን ለጊዜው ደስ ብሎን ኹፍለን አልጋ ይዛ ተኛቜ፡፡ ኹቀን ጀምሮ እንደተመለኚትነው አሁንም ደም ይፈሳትል ዚምጥ ስሜት ዚተናነቃታል፡፡ መርዳት ባለመቻላቜን እያዚን አዝነን
ጥለን ወጣን፡፡ ኚዚያ በኋላ መግባት እንደማንቜልም ተነገሚን፡፡ እስኚ ለሊቱ 9፡15 ድሚስ በምን ሁኔታ ላይ እንዳለቜ ማወቅ አልቻልንም በትግስት ተቀምጠን ጠበቅን፡፡ ዘጠኝ ሰዓት ኚሩብ ሲሆን ንድ ወንድና አንድ ሎት ልጅ በሠላም መገላገሏን ለእሷ ዚተመደበቜውና ቆማ ድራማውን ዚምትኚታተለዋ ሐኪም አበስሚቜን፡፡ ለልጆቹ ልብስ ጠዚቀቜንፀ
ይዘን ስለነበሚ ሰጠናት፡፡ ማዚት እንቜል እንደሆነ ጠዹቅን ቆይ አሁን ትሚጋጋ ብላን ሄደቜ፡፡ ኚንጋቱ 12 ሰዓት ሲሆን አሁንም ማዚት እንድንቜል ጠዹቅን አሁን ዚሚያስፈልጋት አጥሚት ስለሆነ አምጡላት አሉንፀ ሰጠናት፡፡ እኛ ደግሞ አንድ ቀን ሙሉ ደም ሲፈሳት ስለዋለቜ ልባቜን ሊሹጋጋ ባለመቻሉ ማዚት ፈለግን አልፈቀዱልንም ዚሰጠናትን አጥሚት ትጠጣም አትጠጣም ያወቅነው ነገር ዚለም፡፡ ሀኪሟ ተመልሳ መጥታ በጣም በጥሩ ሁኔታ ላይ ናት ኹ2-7 ሰዓት ትወጣለቜ አለቜን፡፡ ሁላቜንም በጣም ደስ አለን፡፡ በዚአቅጣጫው እዚደወልን ለዘመድ አዝማድ ተናገርንፀ ይዘናት ለመውጣት ስንዘጋጅ ትንሜ ደም ስለፈሰሳት ደም ያስፈልጋታል አሉን፡፡ ሁላቜንም ዚእህታቜንን ህይወት ለማትሚፍ ወደ ስታዲዚም አካባቢ ደም ለመስጠት ቀይ መስቀል ሄድን ፡፡” በማለት ያስሚዳሉ፡፡ አክለውም “ሟቜ እህታቜን ኹዚህ በፊት ሁለት ጊዜ በቀት ውስጥ ወልዳለቜ፡፡ ዚመጀመሪያ ልጇ 17 ዓመት ኚሁለት ወሩ ሲሆን ሁተኛዋ ልጇ 16 ዓመቷ ነው፡፡ ሁለተኛዋ ልጇ ተደብቃ ገብታ እናቷን ስትመለኚት በጀርባዋ ተንጋላ ተኝታለቜ
አያኗም ተጫፍኗል፡፡ ብላ ነገሚቜን፡: እኛ ደም ለመለገስ ስንሯሯጥ ዹ17 ዓመት ኚሁለት ወር ዹሆነውን ልጇን አስፈርመው አፕራሲዮን አደሹግን አሉን፡፡ ኚኊፕራሲዮን በኃላ መሞቷ ተነገሚን፡፡ በምን ምክንያት ኊፕራስዮን ልትሆን እንደቻለቜ ሊያስሚዱን አልቻሉም ዕድሜው 18 ዓመት ያልሞላ ልጅ ለምን ማስፈሚም ፈለጉ?፡፡ አስክሬን ለማስሚኚብ
እና ገንዘብ ለመቀበል ይህ ነው ዚማይባል በደል ደርሶብናል፡፡ አስክሬን ለማውጣት ገንዘብ ለመክፈል በሊፍት ውስጥ ዚገባውን ባለቀቷን መብራት ጠፍቶ ለ30 ደቂቃ በአዹር እጥሚት ተዳክሞ በብሚት ታግለንና ሊፍቱን ፈልቅቀን ስናወጣው ዚሊፍት ሠራተኛው እሚፍት ሄዷል መብራት ስለጠፋ ነው ብለው አላግጠዋል፡፡
አስክሬኑን ኚወሰድን በኋላ ኹፍተን ስንመለኚተው ዹተኹፈተው አካሏ በአግባቡ አለመሰፋቱን ማዚት ቜለናል፡፡ እህታቜን ዚሞተቜው በሐኪሞቜ ጥፋት ነው፡፡ ዚተፈጞመብንን በደል ህዝብና ዹሚመለኹተው ዚመንግስት አካል ይወቅልን፡፡” ሲሉ ፍኖተ ነፃነት ጋዜጣ ዝግጅት ክፍላቜን ድሚስ በመምጣት አስሚድተዋል፡፡
በጉዳዩ ላይ ዚጥሩነሜ ቀጂንግ ሆስፒታል  ኃላፊዎቜ አስተያዚት እንዲሰጡበት ተመላልሰን ጥያቄ አቅርበን ነበር፡፡ በተሰጠን መልስም “በዚህ ጉዳይ መልስ መስጠት ዚሚቜሉት ኃላፊ ዚሉምፀ ጥያቄውን በደብዳቀ መጠዹቅ አለባቜሁፀ ኚመምጣታቜሁ በፊት ስልክ ደውሉልን” በሚል ምክንያቶቜ ዚሆስፒታሉን አስተያዚት ማካተት አልቻልንም፡፡ በጉዳዩ
ላይ አስተያዚት መስጠት ዚሚቜል አካል ቢኖር አሁንም መግለጜ እደሚቜል ዝግጅት ክፍሉ ያሳውቃል፡፡

↧

ዚማን቞ስተር ዩናይትድ አስገራሚ አቋም (ሻምፒዮን ሆነ)

0
0

man 1

man 2

man 3

man 4

man 5

man 6ማን.ዩናይትድ ዛሬ ኊልትራፎርድ ላይ አስቶንቪላን በሮበን ቫንፐርሲ 3 ጎሎቜ በዜሮ አሾንፎ ፕሪምዚር ሊጉን ለ20ኛ ጊዜ አሞንፏል። ዹማን.ዩናይትድን ሲዝን በትንሹ ዚሚዳስስ አጭር ዝግጅት ኹዘ-ሐበሻ ተዘጋጅቷል ይኚታተሉት።
ማን቞ስተር ዩናይትድ ኚሰንደርላንድ ጋር ባደሚገው ጚዋታ ላይ ሮቢን ቫን ፔርሲ ጎሉን ለማስቆጠሩ እርግጠኛ ነበር፡፡ በስታዲዚም ኩፍ ላይት ዚውጀት መመዝገቢያ ላይ ግን ጎሉ ዹተቆጠሹው በተጋጣሚው ተጫዋቜ ታዚተስ ብራምብል መሆኑ ተፃፈ፡፡ በራስ ላይ ዹተቆጠሹ ጎል ተደርጎ መውሰዱ ቫን ፔርሲ ያለ ጎል አልባ ደቂቃዎቜ መጚመራ቞ውን ቀጠለ፡፡ ሆላንዳዊው በክለቡ ማሊያ በመጚሚሻ በተጫወተባ቞ው 10 ሰዓታት አንድ ጎል ማስቆጠር ተስኖታል፡፡ ለ594 ደቂቃዎቜ ማለት ነው፡፡ በዚህ ወቅት ላይ ማን቞ስተር ዩናይትድ ኚኀፍ.ኀ.ካፕ እና ኚቻምፒዚንስ ሊግ ውጭ ቢሆንም በፕሪሚዚር ሊጉ ላይ ሰንደርላንድን ድል በመንሳት ለሰባተኛ ተኚታታይ ጊዜ አሾንፎ ወጥቷል፡፡ ዚቡድኑ ዚውድድር ዘመን ዹሊጉ ምርጥ ብቃት በታዚበት ሰሞን ኮኚቡ ጎል አግቢያ቞ው በጎል ድርቅ መመታት አስገራሚ ቢሆንም ዹሚነግሹን ነገር አለ፡፡ ቡድኑ በሌሎቜ ቊታዎቜ ብቃቱን ማሳደጉን ያሚጋግጥልናል፡፡
ቻምፒዚንስ ሊግ እጅግ አጓጊ በሆነ ደሹጃ ላይ ባለበት በዚህ ዚሩብ ፍፃሜ ወቅት አንድም ዚእንግሊዝ ክለብ አይገኝበትም፡፡ ይህ ሲሆን ኹ1996 ወዲህ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው፡፡ ሰር አሌክስ ፈርጉሰን ቡድና቞ው ዚማይዋዥቅ ብቃቱን ዚሚያበሚክት ጎል አስቆጣሪ አለመያዛ቞ው ያስቆጫ቞ዋል፡፡ ኚሪያል ማድሪድ ጋር በተደሚጉት ዚደርሶ መልስ ጚዋታዎቜ ላይ ጎል ማስቆጠር ዚቻለው ዚዩናይትድ ተጚዋቜ ዳኒ ዌልቀክ ብቻ ነው፡፡ ቫን ፔርሲ ኚስፔኑ ኃያላን ጋር አልቀናውም፡፡ ኹዚህም በኀፍ.ኀ.ካፑ በደርሶ መልሱ ዚቌልሲ ግጥሚያ ቫንፔርሲ በተጠባባቂነት ተቀይሮ ገብቶም ዹፈዹደው ነገር ዚለም፡፡ በውድድር ዘመኑ መጀመሪያ ላይ አላቋርጥ ብሎ ዹነበሹው ዹጎል ፍሰት በዚህ ወሳኝ ወቅት ላይ ሊመለስለት አልቻለም፡፡ ኚቅርብ ጊዜ ወዲህ ዚቀድሞው ዹአርሰናል አጥቂ ለ622 ደቂቃዎቜ በሜዳ ላይ ቆይቶ አንድ ጎል ብቻ አግብቷል፡፡ ኚዚያ ፊት ግን በአማካይ በዹ99 ደቂቃው አንድ ጊዜ ኳስና መሚብን ያገናኘ ነበር፡፡ ምናልባት ለሁለት ተኚታታይ ዚውድድር ዘመናት ለዚክለቊቹ ኹሞላ ጎደል በሁሉም ጚዋታዎቜ ላይ ዹመሰለፉ ነገር አድክሞት ሊሆን ይቜላል፡፡ አምናም ሆነ ዘንድሮ አርሰናል እና ማን቞ስተር ዩናይትድ በቫን ፔርሲ ላይ ተመርኩዘው መቅሚባ቞ው ግልጜ ነው፡፡
በተለይ አርሰናል ለውጀታማነት በተለይ ቫን ፔርሲ ላይ ዹተንጠላጠለ መሆኑ ጉልህ ነበር፡፡ ዘንድሮ ያለ እርሱም ምን ያህል ጥንካሬው እንደላሞቀ ታይቷል፡፡ በማን቞ስተር ዩናይትድ ዌይን ሩኒ ጎል ዚማስቆጠር ሾክሙን አግዞት 12 ጎሎቜን አስቆጥሯል፡፡ ስምንት ጎሎቜን ያገባው ሃቪዬር ሄርናንዮዝም ዹሾክሙ ሌላው ተካፋይ ነው፡፡ ይሁን እንጂ ሺንጂ ካጋዋ በቅርቡ በኖርዊቜ ሲቲ ላይ ሃት ትሪክ ኚመስራቱ በፊት ኚቫን ፔርሲ ቀጥሎ ዚዩናይትድ ኹፍተኛው ጎል አግቢ ፓትሪክ ኀቭራ (4)፣ ጆኒ ኢካንስ (3) እና ራፋኀል ዳ ሲልቫ (3) ነበሩ፡፡ አማካይ ክፍሉ ጎል ዚማስቆጠር እጥሚት ገጥሞት ነበር፡፡ አሁን ደግሞ ቫን ፔርሲ በድርጊቱ ተመቷል፡፡ በተለይ አንቶኒዮ ቫሌንሲያ፣ ሉዊስ ናኒ እና አሜሊ ያንግ ለቜግሩ ኃላፊነት ሊወስዱ ይገባል፡፡ ሶስቱ አማካዮቜ ባለፈው ዚውድድር ዘመን በፕሪሚዚር ሊጉ ላይ በድምሩ 18 ጎሎቜን አስቆጥሚው ጎል ዹሆኑ 30 ኳሶቜን አቀብለው ነበር፡፡ ዘንድሮ ግን ሶስቱ በድምሩ አንድ ጎል ብቻ ያስቆጠሩ ሲሆን ያቀበሏ቞ው ጎል ዹሆኑ ኳሶቻ቞ው ብዛት ዘጠኝ ብቻ ና቞ው፡፡ ሪያል ማድሪድ እና ቌልሲ ማን቞ስተር ዩናይትድን ኚቻምፒዚንስ ሊግና ኚኀፍ.ኀ.ካፑ ሲያስወጡት ዚፕሪሚዚር ሊግ ተጋጣሚዎቜ ግን ዚኊልድትራፎርድ ክለብ ለ20ኛው ዋንጫ እንዲተም ፈቅደውለታል፡፡ ቡድኑ በዚህ ወቅት በፕሪሚዚር ሊጉ ላይ እጅግ ደካማ ብቃት ካላ቞ው ቡድኖቜ መካኚል ሁለቱን (ሬዲንግ እና ሰንደርላንድ) ገጥሞ ኚብዙ ልፋት በኋላ ሁለቱንም ማሾነፍ ዚቻለው 1-0 ብቻ ነው፡፡ ሬዲንግ ኚዩናይትድ ጋር ኚመጫወቱ በፊት ባደሚጋ቞ው ስድስት ግጥሚያዎቜ ሁሉ ዹተሾነፈ ቡድን ሲሆን ሰንደርላንድ ደግሞ ኚስምንት ተኚታታይ ጚዋታዎቜ አንድም ድል ያልተቀዳጀ ነበር፡፡
በውድድር ዘመኑ መጀመሪያ ማን቞ስተር ዩናይትድ ኚሚቆጠሩበት ጎሎቜ ይልቅ በእጥፍ ለሚበልጡ ጊዜያት ጎል ያስቆጥር ነበር፡፡ ኚቫን ፔርሲ ብቃት መቀዝቀዝ በኋላ ግን ይህ ሊሆን አልቻለም፡፡ ዚሚያስቆጥራ቞ው ጎሎቜ ቢያሜቆለቁልም (በሊጉ ላይ) ሜንፈት አልገጠመውም፡፡ ዹዚህ አብይ ምክንያት ዚቡድኑ ዚተኚላካይ መስመር ጥንካሬ መጹመር ነው፡፡ ሰር አሌክስ አጥቂያ቞ው ጎል ማምሚት ሲያቆም ተኚላካያ቞ው ብቃቱን አሳድጎ ኚሜንፈቶቜ ታድጓ቞ዋል፡፡ ለ627 ደቂቃዎቜ አንድም ጎል ሊቆጠርበት አልቻለም፡፡
በግብ ጠባቂነቱ ቊታ በውድድር ዘመኑ መጀመሪያ ላይ ዎቪድ ደ ሂያ ቋሚ ተሰላፊነቱን ለአንደርስ ሊንዎጋርድ አሳልፎ ሊሰጥ እንደሚቜል ዚሚያስጠሚጥር ብቃት ነበሚው፡፡ ሆኖም በራስ መተማመኑ ኚውጀታማነት ጋር በማሳደግ አሁን ቋሚነቱን በአስተማማኝነት ይዟል፡፡ በጚዋታዎቹ ላይ ዚሚፈጜማ቞ው ስህተቶቜ ቁጥር ቀንሰዋል፡፡ አሁንም በራስ መተማመኑ ሚገድ ኹዚህም በላይ መጎልበት ያለበት ሲሆን በተለይ በክሮሶቜ ወቅት ያለው በቃላት ዚሚታማ መሆኑ ቀጥሏል፡፡ ዹጎል ሙኚራዎቜን በማዳር ሚገድ ያስመዘገበው አሃዛዊ ብቃት በሊጉ በአንደኛ ደሹጃ ላይ አስቀምጊታል፡፡ ወጣቱ ስፔናዊ ላይ ኚሚሞክሩት ዹጎል ሙኚራዎቜ 78% በመቶ ያህሉን ያድናል፡፡ በሊጉ ክለቊቜ በቋሚ ተሰላፊነት ኚሚጫወቱት በሚኞቜ ሁሉ ምርጡ ንፀሬ መሆኑነው፡፡ ብዙ ዚእግርኳስ አፍቃሪዎቜ በዮ ሂያ ላይ ተስፋ ሲቆርጡ ሰር አሌክስ ግን በእርሱ ፀንተው ቀመራ቞ው በመጚሚሻ ፍሬውን ማፍራት ጀምሯል፡፡
በተኚላካዩ መስመር ሪዮ ፈርዲናንድ ተደናቂ ብቃቱን መልሶ አግኝቶታል፡፡ ዚኔማኒያ ቪዲቜ ኚጉዳት መመለስ በመሀል ተኚላካይነት ቊታ ላይ ኚአቫንስ ጋር ለተሰላፊነት ኚባድ ፉክክር ውስጥ አስገብቷ቞ዋል፡፡ ዹዚህ ጀናማ ፉክክር ውጀት ደግሞ ዚማን቞ስተር ዩናይትድን ዹኋላ መስመር በቀላሉ ዚማይጣስ አድርጎታል፡፡ በርካታ ጚዋታዎቜን ምንም ጎል ሳይቆጠርባ቞ው መውጣት ቜለዋል፡፡ ይህም ሰር አሌክስ ፈርጉሰን ዹሊጉን ንግስና መልሶ ወደ ኊልድ ትራፎርድ ያመጡ ዘንድ ምክንያት ሆኗ቞ዋል።

ዚዩናይትድ አጥቂዎቜ ዚዘንድሮ ዹጎል ስታቲስቲክስ
ቫን ፔርሲ ሩኒ ሄርናንዮዝ ዌልቀክ ማን ዩናይትድ
- ጎሎቜ 22 12 8 1 66
- አንድ ጎል ለማግባት ስንት ጊዜ ኳስ ጋር ይገናኛል? 68.26 104.66 38.87 656 329.93
- በዚስንት ደቂቃዎቜ አንድ ጊዜ ጎል ያስቆጥራል? 126.47 132.66 85.5 1113 450
- ዚመጚሚሻ ዹሊግ ጎሉን ካስቆጠሚ በኋላ ዚተቆጠሩት ደቂቃዎቜ 332 69 113 702 69
ዹጎል ዕድልን ወደ ጎልነት ዹመቀዹር ንፃሬ 17.27% 15.78% 24.24% 2.77% 14.53%

↧
Viewing all 15006 articles
Browse latest View live